У нас вы можете посмотреть бесплатно መልክአ ጊዮርጊስ ወስንክሳር ዘወርዓ ጥር 23// እንኩዋን ለቅዱስ ጊዮርጊስ እና በእለቱ ታስበውና ተከብረው ለሚውሉት ጻድቃን ሰማዕታት በዓል በሰላም አደረሳችሁ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
#famfan3 #ethiopianorthodox #ethiopia #duet #habesha #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ከሐዲውን ንጉሥ ዱድያኖስ ጨምሮ ሰባ ነገሥታት ቅዱስ ጊዮርጊስን በልዩ ልዩ መከራ አሰቃይተውታል። ሦስት ጊዜ ቢገድሉትም ጌታችን ከሞት እያስነሣው ከሐድያንን አሳፍሯቸዋል፡፡ ቅዱሱን መግደል ያልተቻለው ንጉሥ “አጥንቱን ንፋስ እንዲወስደው በመንኰራኩር ፈጭታችሁ በይድራስ ተራራ ላይ በትኑት” በማለት አዘዘ፡፡ ወታደሮችም ቅዱስ ጊዮርጊስን በመንኰራኩር ፈጭተው በተራራ ላይ ቢበትኑት እራሩ ያረፈበት ሣር ቅጠል ሁሉ “ጊዮርጊስ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር፣ ጊዮርጊስ ሰማዕቱ ለእግዚአብሔር” በማለት ቅድስናውን ገልጧል ፡፡ ጌታችን ሰማዕቱን ለሦስተኛ ጊዜ ከሞት አስነሣው። አጥንቱን አድቅቀው በማቃጠል በተራራ ላይ በትነውት ነገሥታቱ ወደ ነበሩበት በመመለስ ላይ የነበሩትን ወታደሮች “ እናንተ ወታደሮች ጠብቁኝ” አላቸው፡፡ ወታደሮቹ ዘወር ብለው ቢመለከቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነው። በጣም ደንግጠው እንዴት ከሞት ልትነሣ ቻልክ በማለት ጠየቁት። “አምላኬ ከሞት አስነሣኝ” አላቸው፡፡ ጭፍሮቹም ከእግሩ ሥር ወድቀው በአምላክህ እናምናለን አሉት። ቅዱስ ጊዮርጊስም አምላኩን ቢለምነው ውሃ ፈለቀለት። አዳዲስ አማንያንንም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ተገልጦ አጥምቋቸው ተሰወረ፡፡ እነርሱም በነገሠታቱ ፊት ስለጌታችን በመመስከር በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ አጥንቱ ተፈጭቶ ከተቃጠለ በኋላ በይድራስ ተራራ ላይ ቢበተንም በአምላኩ ቸርነት ተነሥቶ በከሐድያን ፊት በጽናት እየመሰከረ ብዙዎችን #ክርስቶስን ወደ ማመን የመለሳቸው የቅዱስ ጊዮርጊስ በረከት ይደርብን፡፡ አሜን ። ቅዱስ ጊዮርጊስ