У нас вы можете посмотреть бесплатно የገዳማውያኑ ውሎ እና አዳር или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ጥንታውያን ገዳማት አንዱ ነው። ይህ ገዳም በሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዐፄ ገብረ መስቀል የመጀመሪያው ቤተ ክርስቲያን የተሠራበት ሲሆን ይህ ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ ያሬድ ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ እንደ ተከበረ የገዳሙ ታሪክ ያስረዳል። ዐፄ ገብረ መስቀል በቦታው ያሠሩት ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ሲሆን ይህ ቤተ ክርስቲያን በዮዲት ጉዲት ዘመን ተሰውሯል። ከዚህ ጊዜ በኋላ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወደ ኢትዮጵያ እስከሚመጡበት እስከ አሥራ ሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን እግዚአብሔር በሚያውቃቸው ስውራን ቅዱሳን ሲጠበቅ ቆይቶ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ የተጋድሎአቸው ቦታ ሆኖ ብዙ ተጋድሎ ፈጽመውበታል። አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በቦታው ላይ በሚገኘው ትልቅ ባሕር (ሐይቅ) ውስጥ ለመቶ ዓመታት በጭንቅላታቸው ተዘቅዝቀው ቆመው ጸልየውበታል። ባሕሩም ጸበል ሆኖ እስከ ዛሬ ድረስ ፈውስ እየሰጠ ይገኛል። አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከዚህ ዓለም ድካም ካረፉ በኋላ በዐፄ ሕዝበ ናኝ ዘመን አምስት አብያተ ክርስቲያናት በቦታው ላይ ተተክለው ነበር። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናትም የመድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ቤተ ክርስቲያን፣ የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን፣ የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እና በጴጥሮስ ወጳውሎስ እና በአባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስም የሚጠራ ቤተ ክርስቲያን ነበር። በግራኝ አሕመድ ወረራ ጊዜ እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል። በንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት እንደገና ገዳሙ መልሶ ሊቀና ችሏል። ገዳሙ እስከ ዛሬ ድረስ የፈውስ እና የድሕነት ገዳም ሆኖ ይገኛል። ገዳሙ የአንድነት ገዳም ሲሆን ብዙ መናንያን ይገኙበታል። ከዚህ በላይ ስውራን ቅዱሳን የሚገኙበት ገዳም ነው። The Zequala Debre Kewakibt Abune Gebre Menfes Kidus Monastery is one of the ancient monasteries found in Ethiopia. According to the monastery’s history, the first church on this site was built in the 6th century (7th century EC) by Emperor Gebre Meskel, and its consecration was blessed by Saint Yared. The church built by Emperor Gebre Meskel was dedicated to Egziabher Ab (God the Father), but it was hidden (became mystical/invisible) during the era of Yodit Gudit. From that time until the 12th century, when our father Abune Gebre Menfes Kidus arrived in Ethiopia, the site remained protected by "hidden saints" known only to God. When Abune Gebre Menfes Kidus came to Ethiopia, he chose this location for his spiritual struggle and performed many great feats of asceticism there. Our father prayed for 100 years while standing upside down in the large lake (crater lake) found at the site. That lake became holy water (Tsebel) and continues to provide healing to this day. After our father Abune Gebre Menfes Kidus rested from the labors of this world in the 14th century, five churches were established on the site during the reign of Emperor Hizba Nañ. These churches were: Medhane Alem (Savior of the World), St. Mary, St. Michael, St. Gabriel, and a church named after Saints Peter & Paul and Abune Gebre Menfes Kidus. These churches were destroyed during the invasion of Gragn Ahmed. However, during the reign of King Sahle Selassie, the monastery was successfully restored. To this day, it remains a place of healing and salvation. It is a monastery of "Andinet" (communal living/unity) where many monks reside. Furthermore, it is a monastery where hermit saints are said to be found.