У нас вы можете посмотреть бесплатно ልዩ ትምህርት የዘር ማንዘራችን የኋላ ታሪክ ከጣኦት ጋር የተገናኘ ነው! በመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ Memehir Girma Wondimu или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
#ሁላችንም_ልንማርበት_የሚገባ_ወቅታዊ_ልዩ_ትምህርት_Subscribe_Share_like_በማድረግ_አገልግሎቱን_ይደግፉ። ክፉው መንፈስ (አውሬው) ዛሬ በዓለም እንዲነግሥ ርስቱን ከማመቻቸቱ በፊት፤ ለዘመናት የተጠመቀ የሐሰት ወይን ጠጅን በተለያየ መንገድ ሲያጠጣን ከርሞአል፡፡ ኢየሱስን ብቻ አይደለም መጥምቁ ዮሐንስ የሚቀድመው፡፡ ሐሣዊውም መሢሕ የራሱ መንገድ ጠራጊ አለው፡፡ እኛ እንዲህ ከመሆናችን በፊት፥ እንዲህ መሆናችንን የሚያዘጋጁ፣ የሚያስተምሩ፣ ተራራዎችን (ጽድቆችን) የሚያስጎነብሱ፣ ሸለቆዎችን (ርኩሰቶችን) የሚሞሉ ቃላትን በአይነተ ብዙ አውታሮች ተቀብለናል፡፡ ከነዚህ አውታሮች መካከል የአስኳላው ትምህርትና የመዝናኛው ኢንደስትሪ ዘርፍ በዋነኝነት ይጠቀሳሉ፡፡ መጽሐፍ ስለ አውሬው መልክና ማንነት በዝርዝር ይናገራል ፦ "ሌላ አውሬ ከባሕር ሲወጣ አየሁ አለ፤ ሐሣዊ መሢሕ ነው፡፡ መንግሥቱ ገና አልተደላደለምና እምባሕር አለ፡፡ .. ዐሥር ቀንዶች ያሉት ሰባት አርእስት ያለው፤ በዐሥር ቀንዶቹ ላይ ዐሥር ትርፍ ያለው አንድም ያን ጊዜ ይሾማል አንድም የእኔ ናቸው ይላል፤ ያለቃ አለቃ ያሉት ያን ጊዜ ይሾማል፤ አንድም የእኔ ናቸው ይላል፡፡ በሰባቱ አርእስት ላይ የስድብ ስም ተጽፎበታል አለ፤ አምላክ ነኝ ይላል፡፡ አንድም ሰባቱ አርእስተ ኃጣውኡ በሱ ጊዜ ይሠራሉ፤ ኃጢአተ አዳም፣ ቅትሌተ አቤል፣ ጥቅመ ሰናዖር፣ ኃጢአተ ሰዶም፣ ኃጢአተ እስራኤል፣ ቅትሌተ ዘካሪያስ፣ ሞተ ወልደ እግዚአብሔር፡፡ አንድም ሰባቱ አህጉር ያመልኩታል፤ ፋርስ፣ ባቢሎን፣ ፅርዕ፣ ሜዶን፣ ግብፅ፣ ሮም፣ ኢየሩሳሌም"