У нас вы можете посмотреть бесплатно ጴርጋሞን | ሰባቱ የእስያ አብያተ ክርስቲያናት | ፓስተር አስፋው በቀለ | www.operationezra.com или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
የጴርጋሞን ከተማ ከሰምርኔስ በስተሰሜን 100 ኪሎ ሜትሮች ያህል ርቃ የምትገኝ ሲሆን፥ ምናልባትም ከዮሐንስ የተላከው መልእክተኛ የሚጎበኛት ሦስተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን ሳትሆን አትቀርም። ጴርጋሞን የእስያ አውራጃ ርእሰ ከተማ ስትሆን፥ የዙስ ጣዖት የሚመለክበት ትልቅ ቤተ መቅደስ እና መሠዊያ ይገኝባት ነበር። በተጨማሪም፥ የንጉሥ አምልኮ ይፋዊ የነበረበት ማዕከል ነበረች። ከዚህ ጠንካራ ሐሰተኛ አምልኮ የተነሣ ክርስቶስ ከተማይቱ የሰይጣን ዙፋን የሚገኝባት እንደሆነች ገልጾአል። ክርስቶስ ራሱን ስለታምና በሁለት ወገን የተሳለ ሰይፍ እንደያዘ አድርጎ ገልጾአል። ይህም ክርስቶስ ወደዚያች ቤተ ክርስቲያን የሰላምን ቃል ሳይሆን ፍርድን ይዞ እንደሚመጣ ያሳያል። ክርስቶስ መልእክቱን የጀመረው የምሥጋና ቃል በማስተላለፍ ነው። ቤተ ክርስቲያኒቱ በስደት ጊዜ ክርስቶስን አልካደችም ነበር። ምንም እንኳን ከአባሎቻቸው አንዱ የሆነው አንቲጳስ ቢገደልም፥ በእምነቷ ለመጽናት በቅታለች። ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደምንረዳው፥ አንቲጳስ ከመጀመሪያዎቹ የእስያ ሰማዕታት አንዱ ነበር። የቤተ ክርስቲያን አፈ-ታሪክ እንደሚያወሳው ይህ ሰው እስከነ ሕይወቱ በበርሜል ውስጥ ተቀቅሎ እንዲሞት ተደርጓል። እንደ ክርስቶስ (ራእይ 1:5)፥ ይህ አማኝ የታመነ ምስክር ነበር። ሕይወቱን እስከ መስጠት ድረስ በእምነቱ ጸንቶ ቆሟል። ይሁንና በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ብዙ የተሳሳቱ ነገሮች ነበሩ። ልክ በለዓም ምድያማውያን ሴቶቻቸውን ወደ አይሁዳውያን በመላክ በወሲብ ኃጢአትና የጣዖት አምልኮ እንዲወድቁ እንዳደረገ ሁሉ፥ በዚህች ቤተ ክርስቲያን ውስጥም ሌሎች የቤተ ክርስቲያን አባላትን ወደ ጣዖት አምልኮ፥ የወሲብ ኃጢአትና ለጣኦታት ከሚሠዉ ሰዎች ጋር ኅብረት ወደ ማድረጉ ተግባር (ለጣዖት የተሠዋውን ምግብ እንዲበሉ) እየመሩ የቅጣት እርምጃ ያልተወሰደባቸው ሰዎች ነበሩ። ኒቆላውያን አማኞች እምነታቸውን እንዲያለሳልሱ ያስተምሯቸውና ይመክሯቸው ዘንድ ትተዋቸው ነበር። ክርስቶስ እነዚህ ሰዎች ንስሐ ገብተው ኃጢአታቸውን መናዘዝ ብቻ ሳይሆን፥ አኗኗራቸውንም እንዲለውጡ ይነግራቸዋል። ይህ ካልሆነ እንደ ጦረኛ መጥቶ ይወጋቸዋል። ክርስቶስ ዓለምን ላልመሰሉ እና እምነታቸውን በንጽሕና ለጠበቁ አማኞች መናና ነጭ ድንጋይ እንደሚሰጥ ይናገራሉ። ምሁራን – የእነዚህ ነገሮች ትርጉም ምን እንደሆነ ይከራከራሉ። የተሰወረው መና በሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር የሚደረግን ኅብረት የሚያመለክት ይመስላል (አብረን በመመገብ ደስ እንደምንሰኝ ሁሉ ማለት ነው)። ይህም እምነታቸውንና ሕይወታቸውን በንጽሕና የጠበቁት አማኞች ብቻ የሚያገኙት ዕድል ነው። በዮሐንስ ዘመን ነጭ ድንጋይ ለተለያዩ ነገሮች ሊያገለግል ይችላል። አንዳንዶች ነጭ ድንጋይ አንድ ሰው የቤተ መቅደስ ጋለሞቶችን ለመጎብኘት ወይንም በቤተ መቅደስ ውስጥ ለመመገብ በሚሄድበት ጊዜ የሚጠቀምበት እንደሆነ ያስባሉ። ክርስቶስ ግን እርሱ የሚሰጠን ነጭ ድንጋይ ወደ መንሥተ ሰማይ ለመግባትና በዚያም ሲጠባበቁን የነበሩትን በረከቶች እንድንቀበል የሚያስችለን በመሆኑ ታላቅ ዋጋ እንዳለው ይናገራል። አዲስ ስም አዲስ ግንኙነት መኖሩን ያመለክታል። አሁን ንጹሐን ሆነን ብንቆይ፥ በሰማይ ከክርስቶስ ጋር ልዩ ግንኙነት እያደረግን ደስ እንሰኛለን።