У нас вы можете посмотреть бесплатно ኩባንያችን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ኩባንያችን በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት 3.93 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ብዛት 87.1 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ ከእቅድ አንጻር አፈጻጸሙ 101.5% ሆኗል፡፡ ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ6.56 ሚሊዮን ወይም የ8.1% እድገት አሳይቷል፡፡ የደንበኞችን ቁጥር ለመጨመር እና የኔትወርክ ጥራትን ለማሻሻል ከተሰሩ ስራዎች መካከል በግማሽ ዓመቱ 278 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች ተጠናቀው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን፣ (ከእነዚህም 130 የሚሆኑት የገጠር አካባቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው)፤ በሞባይል ኔትዎርክ በተከናወኑ ስራዎች ተጨማሪ 3.21 ሚሊዮን የኔትወርክ አቅም በመገንባት አጠቃላይ ደንበኞችን የመሸከም አቅምን ወደ 108 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል፡፡ በዚህም 133 ተጨማሪ ከተሞች የ4ጂ LTE አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን የቻሉ ሲሆን፤ አጠቃላይ የ4ጂ ተጠቃሚ ከተሞች ቁጥር 1,069 ደርሷል፡፡ በተጨማሪም ማህበረሰቡን የዲጂታል ኢኮኖሚው ተጠቃሚ የሚያደርጉ 204 ምርትና አገልግሎቶች የቀረቡ ሲሆን፤ የቴሌብር ደንበኞች ቁጥርም 58.61 ሚሊዮን ደርሷል፡፡ ኩባንያችን በግማሽ ዓመቱ 85.02 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ በማስገኘት የእቅዱን 81.1% እንዲሁም 88.19 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት የእቅዱን 83% ያሳካ ሲሆን፤ 42.36 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ (EBITDA) ማስመዝገብ ችሏል፡፡ ለተጨማሪ https://bit.ly/45EuiQC #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #GSMA #ITU #Ethiotelecom #GSMA #telebirr #ecommerce