У нас вы можете посмотреть бесплатно እኔ ነኝ የፈጠርኳችሁ……..? የሱ ፍጡር ያልሆናቸሁ ማድመጥ አለባችሁ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
እንዳንፀልይ የሚያደርጉን የአየር አጋንንት እኔ ነኝ የፍትረኳቹ እኔ ነኝ የፈጠርኳችሁ……..? የሱ ፍጡር ያልሆናቸሁ ማድመጥ አለባችሁ በተመስጦ መጸለይ ለምን አቃተን? /የአየር አጋንንት በጸሎት…/ በጸሎት ሰዓት ሐሳባችን ለምን ይበተናል? ለምን በተመስጦ መጸለይ አቃተን? ለሚሉት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠታችን መፍትሄ ከማበጀታችን በፊት የጸሎት ግብአት ወይም መስፈር የሚሆኑትንት እስከ ክፍል ስምንት አይተናል፡፡ አሁን ደግሞ የችግራችንና የጥያቄአችን መልስ ወደ ሆነው እንሄዳለን፡፡ አንድ ሰው ጸሎትን ሐሳቡ ሳይከፋፈል፣ሌሎች የሐሳብ ማዕበሎች ሳያናውጡት ሐሳቡን በመግዛት በተመስጦ ሆኖ እንዳይጸልይ ከሚያደርጉት እንቅፋቶች ውስጥ ምን ምን ናቸው? ከሚሉት ውስጥ አንዱና ዋነኛው አጋንንት ነው፡፡ አንድ ሰው በጸሎት ሰዓት ሐሳቡ እየተበታተነ በተመስጦ መጸለይ ካቃተው መበሳጨት ሳይሆን የጸሎትን ኃይል መረዳት አለበት፡፡ ይህ ማለት ጸሎት ስንጸልይ ሐሳባችን ስለተበተነ እግዚአብሔር አይሰማኝም ሳይሆን ጸሎቴን ፈጣሪ ስለሚሰማ ጸሎቴን የሚያደናቅፍ አንድ ኃይል አለ ብሎ ማሰብ አለበት፡፡ ለምሳሌ ልብ ወለድ ስናነብ የሐሳብ መበተን ሳይሆን የሐሳብ መሰብሰብ መመሰጥ ነው የሚታይብን፡፡ ልብ ወለድ ስናነብ መጽሐፉ ያጥርብናል፤ጸሎት ስንጸልይ ግን ይረዝምብናል፡፡ በጸሎት ሰዓት ግን ሐሳባችን ሊዘበራረቅ ይችላል፡፡ ይህም የሚሆነው አጋንንት ልብ ወለድ ስናነብ ሳይሆን በጸሎት ሰዓት መጥተው እንደሚፈትኑን ማሳያ ነው፡፡ ልብ ልንለው የሚገባ እግዚአብሔር ፊት ለጸሎት ቆመን ተመስጦ ካጣን፣ሐሳባችን ከተበታተነብን በግልጽ የሚፈትነን አጋንንት አለ ማለት ነው፡፡ ይህን ሐሳብ የአጋንንት ጥበብ ያልገባቸው ላይቀበሉ ይችላሉ፡፡ በመሰረቱ በጸሎት ሰዓት አጋንንት ነው የሚፈትነን ብንልም አጋንንት ሰይጣን የወል መጠርያቸው ነው፡፡ በስመ አጋንንት ብዙና እንደ ስራቸውና እንደ ተንኮላቸው የተለያዩ ናቸው፡፡ ስለዚህ ሌሎቹን ትተን ለርዕሳችን የሚሆኑትን አጋንንት እንመለከታለን፡፡ 1ኛ/ የአየር አጋንንት ፦ የአየር አጋንንት በጸሎት ሰዓት የሰውን ሐሳብ በመበተን በተለይም የማንፈልጋቸውን ምናልባትም ጸያፍ ነገሮችን በማሳሰብ ከፊልም ባልተናነሰ መልኩ በማሳየት በመፈተን ይታወቃል፡፡ የአየር አጋንንት የሚባሉት በቀደመው ወራት ሳጥናኤል ቅዱሳን መላእክትን ‹‹እኔ ነኝ የፈጠርኃችሁ›› በማለት ሰማያዊ ሽብር ሲፈጥርባቸው መላእክት ለሦስት ተከፍለው ነበር፡፡ የመጀመርያዎቹ የብርሃን መላእክት የሆኑት በቅዱስ ገብርኤል ቃል በመጽናናት ‹‹የፈጠረንን እግዚአብሔርን እስክናውቅ እስክናይ ባለንበት እንጽና›› በሚለው ቃል የጸኑ ናቸው፡፡ እነዚህ ቁጥራቸው ከቅዱሳን ከብርሃን መላእክት ጋር የሆኑ ናቸው፡፡ ሁለተኛው ምድብ በሳጥናኤል ቃል በማመን ‹‹አዎ ሳጥናኤል ነው የፈጠረን›› በማለት ፈጣሪን የከዱ ከሳጥናኤል ጋር በክህደተ እግዚአብሔር የተዛመዱ ናቸው፡፡ እነዚህ ናቸው ሰይጣናት አጋንንት ተብለው የጨለማ ሰራዊት የሆኑት፡፡ ሦስተኞቹ የጸሎት እና የእምነት ጠንቅ የሆኑት ‹‹እግዚአብሔር ነው ወይስ ሰይጣን ነው የፈጠረን?›› ብለው ሳይለዩ በጥርጥር የታዩ ናቸው፡፡ በቅዱስ ገብርኤል ቃል የጸኑት እግዚአብሔር ነው የፈጠረን ያሉት ብርሃናውያን መላእክቶች ክብርን ተጎናጽፈው ከእግዚአብሔር ጋር በሰማይ ሲቀሩ የካዱት ተዋርደው ከሳጥናኤል ጋር ወደ ሲኦል ወርደዋል፡፡ ሦስተኛቹ ተጠራጣሪዎቹ ግን ከእግዚአብሔርም ከሳጥናኤልም/ከሰማይም ከሲኦልም/ ሳይሆኑ በአየር ላይ ቀርተዋል፡፡ ግን ተጠሪነታቸው ለሳጥናኤል መሆኑን ልብ በሉ፡፡ ምክንያቱም ሳያምኑ መጠራጠር ከሳጥናኤል ጋር የሚያስደምር ስለሆነ ከእሱ ጋር ተቆጥረዋል፡፡ እነሱም የአየር አጋንንት ተብለዋል፡፡ እስኪ የአየር አጋንን በጸሎት፣በእምነት እና በሌላም ዙርያ እንዴት እንሚፈትኑ እንይ፡፡ ሀ/ በጸሎት የአየር አጋንንት ፈተና፦ የአየር አጋንንት በጸሎት ሰዓት ከሌሎቹ አጋንንት በተሻለ መልኩ የሚፈትኑን በአየር ላይ ስለሚያንዣብቡ በቀላሉ ለእነሱ የተጋለጥን ስለሆነ ነው፡፡ ጸሎታችንን ልክ እንደ ጀመርን በቅጽበት እኛ በማናውቀው ምናልባትም እራሳችን በሚመስለን መልኩ አንድ ሐሳብ ልባችን ውስጥ በማስገባት ወይም የረሳነውን በማስተዋስ ይፈትኑናል፡፡ ለምሳሌ የተጣላነው ሰው፣ያስቀየመን ሰው፣ለሰው ያበደርነው ገንዘን፣የጠፋብን/የረሳነው/ ዕቃ ወዘተ ትዝ የሚለን ጸሎት ላይ ስንሆን ነው፡፡ ይህን የሚያደርጉት የአየር አጋንንቶች ናቸው፡፡ በዚህም ያልፈለግነውን ሐሳብ ከኛ ለማራቅ በምንገጥመው ውስጣዊ ግብግብ ጸሎቱ ይዘነጋናል፣በጸሎት መጽሐፍ የምናደረሰው ምስጋና ይረሳናል፡፡ ምን እንደጸለይን እንኳ ላናስታውስ እንችላለን፡፡ የአየር አጋንንቱ ሐሳቡን ለእኛ ሰጥቶ እሱ ከእኛ ይርቃል እኛን በሐሳብ ከጸሎት ያታግለናል፡፡ የምንፈልገውን ሳይሆን የማንፈልገውን ሐሳብ እናስተናግዳለን፡፡ ይዘን የቆምነውን የጸሎት አላማ በሌላ ይለወጥብናል፡፡ ይህ ታላቅ የአጋንንት ፈተና ቅዱስ ጳውሎስ ስለተሰቃየበት ‹‹የማልወደውን ክፉ ነገር አደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን በጎውን ነገር አላደርገውም፡፡ የማልወደውን የማደርግ ከሆንሁ ግን ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም፣በእኔ የሚኖር ኃጢአት ነው እንጂ›› በማለት አጋንንት ምን ያህል ይፈትነው እንደነበር ከልምዱ እንድንማር ነግሮናል፡፡ /ሮሜ 7÷19-20/ በዚህም በጸሎታችን ተስፋ መቁረጥ እንዲሰማን ‹‹እንዲህ እያሰብኩ ከምጸልይ ቢቀርብኝ ይሻላል›› እንድንል ያደርገናል፡፡ የአየር አጋንንት በጸሎት ሰዓት እኛን መፈተኑ ሁለት ነገር ያስጠቅመዋል፡፡ አንደኛው በጸሎታችን መሃል እየገባ እንዳንመሰጥ፣ተመስጦን እንዳንለማመድ ሲያደርገን ሁለኛውና ዋነኛው በጸሎታችን ተስፋ ቢስ ወይም ተስፋ እንድንቆርጥ ያደርገናል፡፡ የአየር አጋንንት በጸሎት ሰዓት አንድ ሐሳብ በስውር ሹክ ብሎን ይሄዳል በሐሳቡ እኛ እንሰቃያለን፡፡ ወዳጆቼ ምንም በጸሎታችሁ ሰዓት ሐሳባችሁ ባይሰበሰብም ተመስጦ ባይኖራችሁም መጸለይ ማቋረጥ የለባችሁም፡፡ ጸሎታችሁን ተስፋ በመቁረጥ ከተዋችሁ ያኔ ለአጋንንቱ እጅ እንደሰጣችሁ እንደ ተማረካችሁ ቁጠሩት፡፡ ዓላማው ጸሎታችሁን በፈተና ማስተው ነውና ከተዋችሁ አጋንንታዊው ደስታ እንዲኖረው አደረጋችሁት ማለት ነው፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ አንዳንዴ ከንፈር ጸሎትን ቢነዳም ልብ ነገር ቢያሰናዳም ከመጸለይ ወደ ኃላ ማለት አይገባም፡፡ ለዚህም እንድትጽናኑ ሳይሆን እውነቱን በአስረጂ ምሳሌ ልንገራችሁ፡፡ ለምሳሌ አንድ ዓይነ ስውር በበትሩ እየተመራ ውሻ ባለበት መንደር ቢሄድ ውሻው ዝም አይልም፡፡ ይልቁንም እኔን ሊመታኝ ነው በማለት ምንም ያልተነካው ውሻ በዓይነ ስውሩ ላይ ይጮኃል፡፡ ዓይነ ስውሩም ውሻ መከላከያ ሳይሆን መንገድ መምሪያ ትሆነው ዘንድ የያዛት በትር ከውሻ ንክሻ ትታደገዋለች፡፡ ውሻውም ዓይነ ስውሩ የያዛት በትር መመሪያ ሳትሆን እሱን መምቻው ስለምትመስለው ዓይነ ስውሩን ከመንከስ ይልቅ በትርዋን እየፈራ ይጮህበታል፡፡ ዓይነ ስውሩ መንገድ መምሪያው ትሆነው ዘንድ የያዛት በትር ሳያውቀው ከውሻ ንክሻ ትታደገዋለች፡፡ ጸሎታችን ልክ እንደዚህ ነው፡፡ እኛ ወደ እግዚአብሔር ይመራናል፣ጥያቄያችንን ይመልሳል ችግራችንን ያቃልላል ብለን የያዝነው ጸሎት ለአጋንንት እንደ ዱላ ምት ስለሚሆንበት ይረበሻል፡፡ እኛ ወደ እግዚአብሔር ያቀረብነው ጸሎት ለአጋንንት እሳት ስለ ሚሆን በላያችን ላይና በአቅራብያችን ላለው ርኩስ መንፈስ እሳት በመሆን ያቅጥለዋል፡፡ ስለዚህ በየትኛውም የ ሐሳብ መበተንና ውስጥ ብንሆንም በፊቱ ለክፋት ሳይሆን ለጸሎት የቆምንለት ፈጣሪ ስለሚያውቅ ጸሎታችን ይሰማል፡፡ አ0ንድ ሰው በጸሎቱ ሰዓት የአየር አጋንን እየፈተነው እንደ ሆነ በምን ያውቃል? ካልን ግልጽ ምልክቶች አሉት፡፡ ምልክቶቹም በጸሎት ሰዓት የሐሳብ መሰረቅ፣የልቦና መዘበራረቅ፣ተረጋግቶ አለመጸለይ፣እንቅልፍ እንቅልፍ ማለት፣መደበት፣አትጸልይ የሚል ስሜት መሰማት፣ለምን እንደምንጸልይ ግራ መጋባት፣መቁነጥነጥ፣ወገብ አከባቢ ህመም መሰማት፣እጅና በተለይ ሙሉ ሰውነት መዛል፣ትንፋሽ ማጠር፣ማፋሸግ፣እያዛጉ እንባ ማንጠባጠብ፣ድገተኛ እራስ ምታት፣መደንዘዝ፣ምላስ መተሳሰር፣የፍርሃት ስሜት መሰማት፣ጭው የሚል ነገር ውስጥ መግባት፣የልብ ምት መጨመር ወይም መቀነስ፣መንቀጥቀጥ፣ድንገተኛ ሆድ መነፋት፣በፈስ መወጠር ወዘተ ናቸው፡፡ እነዚህ የአየር አጋንንቶች በጸሎት ሰዓታችን ሲፈትኑን የምናያቸው ምልክቶች ስለሆኑ መደነቅ እና መደናገጥ አያስፈልግም፡፡ ግን ከእነዚህ ምልክቶች ውስጥ ግማሾቹ የአይነ ጥላ ምልክቶችም ናቸው፡፡ ሌላ ጊዜ በዝርዝር እናያቸዋለን፡፡ ህሊናችን ልቦናችን ተበትኖ ብንጸልይም ከአንድበታችን የሚወጣው ቃለ እግዚአብሔር ለአጋንንት እሳት መሆኑን አንርሳ፡፡ ጸሎት ማለት በምቾት ውስጥ ሆኖ ሳይሆን በፈተና ውስጥ ሆኖ ሲጸልዩት ነው በረከቱና ዋጋው ከፍ የሚለው፡፡ ጸሎት ምንም እንኳን ተመስጦ ባይኖረውም ከልብ ፍላጎት የሚወጣ ስለሚሆን ተሰሚነቱ አያጠራጥርም፡፡