У нас вы можете посмотреть бесплатно በኤጀንሲዎች ስር ተቀጥረው የሚሰሩ የጥበቃ ሰራተኞች..... или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
የካቲት 11/2018 በአዲስ አበባ ባንኮችን፣ የግል ተቋማትን፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ሌላም ሌላም እንዲጠብቁ ሀላፊነት ወስደው፣ ህጋዊ ፍቃድ ተቀብለው፣ ሰራተኛ ቀጥረው የሚያስጠብቁ የግል ኤጅንሲዎች ቁጥር 250 ደርሷል ተብሏል። በእነዚህ ኤጀንሲዎች ስር ተቀጥረው ዩኒፎርም ለብሰው፣ ዱላ ታጥቀው የሚጠብቁት የመስሪ ቤቱ ንብረት እንዳይዘረፍ፣ ተቋሙ ጥቃት እንዳይደርስበት በር ላይ ቁመው የሚቆጣጠሩ፣ ሰራተኛው ሲገባ ፍትሸው የሚያስገቡ፣ ሲወጣ አይተው የሚሸኙ ካላቸው ሀላፊነት ከተሰጣቸው የስራ ድርሻ አንጻር የሚከፈላቸው ደመወዝ ለእለት ጉርስ የሚበቃ እንዳልሆነ ይጠቀሳል። ብዙዎቹ በየቀኑ በሚሊዮን ሚቆጠር ብር ሲገባ ሲወጣ የሚውልበትን ባንክ እየጠበቅን የምንቀበለው ክፍያ ለቤት ኪራይ የመክፈል አቅም ያለው አይደለም ፡፡ ደግሞም ኤጅንሲዎች ከተቋሙ የሚቀበሉት ብር ብዙ ቢሆንም ለእኛ የሚደርሰን ግን እጅግ ያነሰ ነው ሲሉ ኤጀኒሲዎችን ይኮንናሉ። ኤጀንሲዎች በበኩላቸው ሰራተኞች ደመወዝ ያንሳል ቢሉም ችግሩ የሚዋዋሉት ተቋም ለኤጅንሲው ሚከፍለው ገንዘብ አነስተኛ በመሆኑ ነው ይላሉ። አቶ በላይ ተሰማ ይባላሉ በአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የስራ ስምሪት ፍቃድ ቁጥጥር ቡድን መሪ ናቸዉ። እሳቸው በእርግጥም እንደዚህ ዓይነት ጥያቄዎች እንደሚደጋጥሙ ጠቅሰው ችግሮችን ለመፍታት የተቋሙንና የኤጀንሲዎን የውል ስምምነት በማረጋገጥ እንደሚፈቱ ነግረውናል። 20 80 አከፋፈል ኤጅንሲዎች በፍርድ ቤት አሳግደዉታል ያሉን አቶ በላይ ተሰማ ነገር ግን እንዲህ ዓይነት ችግር ሲፈጠር ምንም ኤጀንሲውን ደሞዝ ጨምር የምንልበት ህጋዊ ስልጣን ባኖረንም ቢያንስ 60 በሞቶና 70 በመቶ አንዲከፍል እንደሚያደርጉ ሀላፊው ጠቁዋል። በ2018 ባሳለፍነው ስድስት ወራት በተደረገ ቁጥጥር ከ70 በላይ የሚሆኑ ኤጄንሲዎች ለፍቃድ ሲሰሩ ስለመገነታቸዉ አስታዉሰዋል። ባለፉት ስድስት ወራትም ባሳዩት የስነ ምግባር ጉድለት 5 ኤጄንሲዎች ታግደዋል ብለዋል። አሁንም ከሰራተኛ መብት ጋር ችግር የሚፈጥሩ ድርጅቶችን ከማገድ አስከ ፍቃድ መንጠቅና በህግ እስከ መጠየቅ የደረሰ እርምጃ እንደሚወስድ በላይ ተሰማ ነግረውናል። ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ገዛ ጌታሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s=2 LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv Instagram: https://shorturl.at/9X4S7