У нас вы можете посмотреть бесплатно ገድለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. 10፥7 "ከኢትዮጵያ ሰዎች ኃጢአት ይልቅ ገድልህ ትሩፋትህ ሃይማኖትህ ስለበለጠ በዚህም ምክንያት ያለ ልክ ያለመጠን የኢትዮጵያ ሰዎች ኃጢአት ተሰረየላቸው፡ ፡ ስለ ሠራኸው መልካም ሥራ ሁሉ ፈጽሜ ይቅር አልኳቸው...." የገድልህን መጽሐፍ የጻፈውም ያጻፈውም ካንተ ጋር በግልጥ ይለፍ፤ የእሳት ባሕርን ይሻገር ማደሪያውም በብርሃን ቤቶች ይሁን፤ ስሙንም ግሩም በሚሆን መንበሬ ላይ እጽፋለሁ። አምኖ ሳይጠራጠር ሳያወላውል መታሰቢያህን ያደረገ የእሳት ባሕርን ይሻገር ያለ ፍርሀትም በፊቴ ይቁም ለተራቡት እንጀራ ቢሰጥ በመጨረሻይቱ ቀን እኔ የሕይወት ኅብስትን እሰጠዋለሁ በዚህም ዓለም አላስርበውም። ለተጠማ ሰው ጽዋ ውኃ ቢያጠጣ እኔ ከሕፃናት ጋር በመንግሥተ ሰማያት መንፈሳዊ ወተትን አጠጣዋለሁ በመታሰቢያ ቀንህ ዕጣን የሰጠ ሰው ቢኖር ኃጢአተኛም ቢሆን እንደ አበው ንጹሕ ይሆናል ለመታሰቢያህ ንጹሕ ሥንዴ የሰጠ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ቁርባን ይቀበላል። በመታሰቢያህ ቀን ዘይት የሰጠ ቢኖር ርስቱ ከአብርሃም ከይስሐቅ ከያዕቆብ ጋር ይሁን መባዕ መብራት ቢያገባ የእሳቱን የጨለማውን ባሕር ከፀሐይ ሰባት እጅ በሚያበራ በዐሥራ ሁለት መብራት [ይለፍ] በበዓልህ የተሰበሰቡትን ከቅዱሳን ጋር በደብረ ጽዮን እሰበስባቸዋለሁ። ከዚህ በኋላ አባታችን ተነሥቶ ጌታችንን እንዲህ ብሎ ለመነው አምስት መቶ ስሳ ሁለት ዘመን ስኖር ውኃ አልጠጣሁም እህል ለመብላት አላሰብኩም የዛፍ ፍሬም አልቀመስኩም ለሰውነቴም ልብስ አልፈለግሁም ራቁቴን ኖርኩ እንጂ በባሕር ውስጥም ከዓሣ ከባሕር ዘንዶና ከአዞ ጋር ኖርኩ ከዛፍ በታችም ከአዕዋፍ ጋር ኖርኩ ከተራራ ወደ ተራራ እየተዘዋወርኩ ከአንበሳና ከነምር ከድብና ከዘንዶ ጋር ኖርኩ። እኔ እለምንሃለሁ እማልድሃለሁ እሺ በለኝ አንድ ሰው ኃጢአት ቢሠራ መታሰቢያዬንም ቢያደርግ ንስሐ ሳይገባ ድንገት ቢሞት ትምርልኝ ዘንድ። መድኅንም ለአባታችን እሺ ምሬልሃለሁ ብሎ መለሰለት፤ ነፍስህ ከሥጋህ ከተለየችበት ከመጋቢት ፭ ቀን ጀምሮ መታሰቢያህን ያድርጉ አሁንስ ወደ ሰማይ ከፀሐይ ሰባት እጅ ወደሚያበራው ወደ ብርሃን ቤት ውጣ እነሆ ዐሥራ ሁለት አክሊላት ሰጥቸሃለሁ። ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል ሦስት አክሊል አቀዳጀው ቅዱስ ገብርኤልም ሦስት አክሊል ሰጠው ሱራፌልም ሦስት አክሊል ሰጡት ኪሩቤልም ሦስት አክሊል ሰጡት። ዳግመኛም እነሆ መብራት ሰጥቸሃለሁ ዐሥር እልፍ በቀኝህ ዐሥር እልፍ በግራህ ዐሥር እልፍ በፊትህ ዐሥር እልፍ በኋላህ እያንዳንዱ ብርሃን ከፀሐይ እጥፍ የሚያበራ ነው። ዳግመኛ እነሆ የብርሃን ድባብ ሰጥቸሃለሁ ዐሥር እልፍ በቀኝህ ዐሥር እልፍ በግራህ ዐሥር እልፍ በፊትህ ዐሥር እልፍ በኋላህ ይሁኑልህ የያንዳንዱም የድባብ ብርሃን ከፀሐይ ብርሃን እጥፍ የሚያበራ ነው። አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ዓመትም ያለ ልብስ ራቁትህን ስለኖርክ የብርሃንን ልብስ እነሆ ሰጥቸሃለሁ አለው። የደስታ ሞጣሕት ሰጠሁህ ዓይነቱ መብረቅ የሚመስለውን እንደ ንስር የሚበሩ ክንፍ ያላቸው ፈረሶችን እነሆ ሰጥቸሃለሁ አለው። አባታችንም ጌታችንን አቤቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድ ሳታስቀር በሙሉ ማራቸው አለው። ጌታችንም አባታችንን እነሆ የኢትዮጵያን ሕዝብ በሙሉ ዐሥራት እንዲሆኑህ ሰጥቸሃለሁ፤ እንደወደድክ ላንተ ይሁኑ መታሰቢያህን ያድርጉ፤ በጸሎትህ ይታመኑ ደስ ብሏቸው ለዘላለም ይኑሩ። አባታችንም እንዲህ አለው፤ ቀድሞ እስከ ዐሥራ አምስት ትውልድ እምርልሃለሁ ብለኸኝ ነበር ልጅ ባይኖራቸው መካን ቢሆኑስ ምን ትሰጣቸዋለህ። ጌታም እኔ ልጅ እሰጣቸዋለሁ ሴቲቱም መካን ብትሆን ለመውለድ ማሕፀንዋን እከፍታለሁ ወንዱም መካን ቢሆን ከሰውነቱ ዘር አስገኝለታለሁ። ዳግመኛም መታሰቢያህን የሚያደርገውን እናት አባቱ ቢሞቱ ወደ ሲኦልም ቢወርዱ ከእሳት ውስጥ አወጣቸዋለሁ ነፍሳቸውን እሰጥሃለሁ ያንተ ገንዘብ እንዲሆኑህ ዐሥራትም ይሆኑህ ዘንድ። መነኩሴውም የሥጋው መርከብ ቢሰበር የሥጋ ጉስቁልና ቢያገኘው እኔ የድንግልና ክንፍ አበቅልለታለሁ ንጽሕናንም አጎናጽፈዋለሁ።" #ethiopia #eotc #tewahedo #duet #orthodox #abunegebremenfesqidus