У нас вы можете посмотреть бесплатно "ብዙ ፍሬ ማፍራት" ክፍል 1 ,ሐዋሪያው ፍፁም ወ/አረጋይ ,2014 በአዲስ አበባ ቤተክርስቲያን አገልግሎት или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
“በሚመጡት ቀናት ያዕቆብ ሥር ይሰዳል፤ እስራኤልም ያቈጠቍጣል፤ ያብባልም፤ በፍሬያቸውም ምድርን ሁሉ ይሞላሉ።” — ኢሳይያስ 27፥6 (አዲሱ መ.ት) እግዚአብሔር ይሄን ቃል ለምን ተናገረን? [ ] 1- ያዕቆብ ማለት አታላይ አሰናካይ ማለት ነው። ያዕቆብ ያላረፈ ሰው በረከትና እረፍት ፍለጋ የሚንከራተት ሰው ምሳሌ ነው። ያዕቆብ ሥር ካልሰደደ ማፍራት አይችልም። ሥር ለመስደድ የሚያስፈልገው እምነት ነው። ኤርምያስ 17 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ “ነገር ግን በእግዚአብሔር የሚታመን፣ መታመኛውም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው። ⁸ በውሃ ዳር እንደ ተተከለ፣ ሥሩንም ወደ ወንዝ እንደ ሰደደ ዛፍ ነው፣ ሙቀት ሲመጣ አይፈራም፤ ቅጠሉም ዘወትር እንደለመለመ ነው፤ በድርቅ ዘመን አይሠጋም፤ ፍሬ ማፍራቱንም አያቋርጥም።” የያዕቆብ ስም መለወጥ አለበት። ስሙ እስራኤል ይባል። እስራኤል ማለት ልኡል፣ ብርቱ፣ ጉልበታም ማለት ሲሆን ያረፈ ሰው ምሳሌ ነው። ያዕቆብ ሥር ሲሰድ ስሙ እስራኤል ይባላል። ያረፈ ሰው ሥር የሰደደ ሰው ፍሬ ያፈራል። ዮሐ.15:1-18 በአዲስ ኪዳን እንደ ቅርንጫፍ በወይን ግንዱ በእየሱስ ሥር እንድንሰድ ይገባል። ክርስቶስ ሁሉ በሁሉ የሆነ ምንጫችን ነው። በእርሱ በክርስቶስ በእውነተኛው የወይን ግንድ ላይ ካልተጣበቅን (ሥር ካልሰደድን) ሚፈለገውን ፍሬ ማፍራት አንችልም። ቆላ.2:6 እውነተኛ የወይን ግን ካለ ትክክል ያልሆነ የወይን ግንድም ስላለ ትክክለኛውን እንምረጥ፤ እሱም ክርስቶስ ነው። ጌታ ቅርንጫፎች ናችሁ ሲለን ትልቅ በረከት ኘው። ያ ብቻም ሳይሆን የማፍራት ሃላፊነትም ጭምር ነው። ፍሬው ምንድነው? ፍሬው አንድ ነው እርሱም ፍቅር ነው!! አንድ ዛፍ አንድ አይነት ፍሬ ብቻ እንደሚያፈራ እንዲሁ እኛም ለሁሉ የሚሆን ፍቅር የመስጠት ሃላፊነት አለብን። ሕይወታችን ለሁሉ የሚማርክ የሚጠቅም ሊሆን ይገባል። ያንን ነው በብዙ እንድናፈራ ጌታ የሰጠን።