У нас вы можете посмотреть бесплатно ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ እየተገነባ የሚገኘውን ባለ አምስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ ያለበትን የሥራ ሂደት ሲጎበኙ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት የሚገነባው ባለ አምስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ የጎበኙ ሲሆን በአጭር ግዜ ውስጥ የመጀመርያ ወለል ሙሌትም ሊከናወን ነው። +++++++++++++++++ #የካቲት_፲፫_ቀን_፳፻፲ወ፰_ዓ.ም (ጅግጅጋ፣ ኢትዮጵያ) ++++++++++++++++++ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሶማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምሥራቅ አርሲ ከህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ፤ በሀገረ ስብከቱ እየተገነባ የሚገኘውን ባለ አምስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ ያለበትን የሥራ ሂደት ጎብኝተዋል። ከብፁዕነታቸው ጋር ሊቀ ካህናት ቀሲስ ኢዮብ ወንድሙ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ትጉሃን ንጉሤ ጸጋየ የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ እና የሀገረ ስብከቱ ሕንጻ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ -ኢንጂነር አቤል ባሳዝነው የፕሮጀክቱ ሳይት ኢንጂነርና የሀገረ ስብከቱ የልዩ ልዩ ክፍል ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ባለፉት ወራት ሲከናወን የቆየው ከመሬት በታች ያለው የግንባታ ሥራ (Sub-structure) ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ፣ አሁን ላይ የአንደኛውን ወለል አርማታ ለመሙላት የኮለን ማቆም እና የዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ብፁዕነታቸው በጉብኝታቸው ወቅት የተመለከቱ ሲሆን፤ እንደ ሀገረ ስብከቱ መርሐ ግብር አስፈላጊው ግብዓት ከተሟላ በቅርብ ቀናት ወስጥ የመጀመርያው ወለል የኮንክሪት ሙሌት ብፁዕነታቸው ባሉበት ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህ ቀደምም በብፁዕነታቸው እንደ ተገለጸው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በሀገረ ስብከቱ የሚታዩ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን እንደሚፈታ የታመነ ሲሆን፣ ዋና ዋና ፋይዳዎቹም፦ • በሀገረ ስብከቱ የአብነት ትምህርትን ለማጠናከር • ገቢያቸው አናሳ የሆኑ አጥቢያዎችን ለመደጎም • የሥራ ዕድል ፈጠራ፦ የሥራ ቦታ ለሚያስፈልጋቸው ምእመናን እና ወጣቶች የሥራ ዕድልን በማመቻቸት ማኅበራዊ አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል። የልማቱ አርበኛና የወንጌሉ ገበሬ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በአርቆ አሳቢነታቸው እና በሳል የአመራር ችሎታቸው በሀገረ ስብከቱ ሰፋፊ ፕሮጀክቶችንና በተለይም ይህንን ግዙፍ ሕንጻ ካስጀመሩበት ጊዜ አንስቶ በጅግጅጋ ምእመናን ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃትን የፈጠሩና መወደድን ያተረፉ አባት መሆናቸውን ሁሉም የሚናገረው ሀቅ ነው። በመሆኑም ለዚህ የሁላችንም ለሆነው ሀለገብ ሕንጻ ስኬት፣ ምእመናን ከአንድ ሠራተኛ የቀን ዋጋ ጀምሮ አቅማችሁ የፈቀደውን በማድረግ በረከት እንድታገኙ ስንል ጥሪያችንን እያስተላለፍን። ለአሁኑ ሙሌት በአስቸኳይ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች፦ 1. ዊንች (የአርማታ መሙያ ሊፍት) 2. 7 ሜትር የሆነ ሳሲ (Sasi) ብራንድ የእጅ ሜትር (2 ፍሬ) 3. 4 ቢያጆ ጠጠር ሲሆን በረከት ለማግኘት የምትፈልጉ፦ • የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000662272756 • አቢሲኒያ ባንክ፦ 215496813 • አባይ ባንክ፦ 3059410945739219 . አሐዱ ባንክ አካውንት ቁጥር 0065710110901 . ኢ-ብር 093 579 9997 መሆኑን እንገልጻለን። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 (የሱማሌ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለሁሉም ይዳረስ ዘንድ share like follow ያድርጉ ቤተሰብ ይሁኑ) ለመከታተል ከታች ያለዉን ሊንክ ይጫኑ 👇👇👇👇👇👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?... #jigjiga_Ethiopia #somale_Dioceses #ሶማሌ_ሀገረ_ስብከት #ሶማሌ jigjiga። #Telegram_https://t.me/+REQaCZ0QCbQwNDZk