У нас вы можете посмотреть бесплатно 🔴 በቀጥታ፡ የዐቢይ ጾም 1ኛ ሳምንት "ዘወረደ" 4ኛ ቀን ሥርዓተ ቅዳሴ | LIVE: ቅዱስ ሚካኤል Great Lent Week 4 (Zewerede) Liturgy или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
፨ የካቲት 12 ድርሳን ቅዱስ ሚካኤል ፨ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም። በየካቲት ወር በአሥራ ሁለት ቀን የሚነበብ ኃያል ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ድርሳን ይህ ነው። ልመናው በረከቱ ከኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ከዚህ ነገር በኋላ በዚህ አገር የሚኖር ሃይማኖቱ የፀና አንድ ድሃ ነበር። በመዓልትም በሌሊትም ይጸልይ ነበር። ቅዱስ ሚካኤልን ጌታዬ ሆይ እዘንልኝ የዕለት ምግብ የዓመት ልብስ ስጠኝ ይለው ነበር። ሰውዬው ግን ሰነፍ ነው። ከቤቱ ወደሥራ አይወጣም ልድከም አይልም የሚያውቀው ሥራ የለም። አንዲት ሰዓት ስንኳ ልሥራ አይልም። ንግድም አያውቅም። ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በሕልም ተገልጦ ወደዚህ ደሃ ሰው መጣ። እንዲህም አለው።እርሻውም ቢሆን ንግድም ቢሆን ጥቂት ሥራ የማትወድ አንተ ሰነፍ ሰው በመዓልትም በሌሊትም ይቅር በለኝ እያልክ እንዴት ትለምነኛለህ። እባርክልህ ዘንድ ወይንህ የት ነው ስንዴህ የት ነው የሠራኸው የትነው የደከምክበት የት ነው። አንተ ሰነፍ ሰው የምተሸጠው የምትገዛበት የት አለ ጌታዬ ሚካኤል እዘንልኝ እንደምን ትለኛለህ። የደከምክበት ሥራ የት አለ። የሁሉ አባት አዳምን እግዚአብሔር እንዳለው አልሰማህምን፡ በክፉ በዲያብሎስ ሽንገላ የአዘዘውን ሕግ በተላለፈ ጊዜ። ይህች የተገኘህባት ምድር ናት ወደሷም ትመለሳለህ። ሥራ በፊትህ ወዝ እንጀራህን ብላ። እሾህ አሜከላ ይብቀልብህ አላለውምን አንተ ግን አትሠራም ግን ባርክልኝ ትለኛለህ። ይህን ብሎ ወደ ሰማይ ወጣ። በነጋ ጊዜም ይህ ድሃ ተነስቶ ሊጸልይ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደ። ሊጸልይም በቅዱስ ሚካኤል ስም ወደ ተሠራው መቅደስ ገባ። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ከኔ ጋር ሁን አትለየኝ አለ። ከቤተ ክርስቲያንም በወጣ ጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈራ ለደሆች ለችገረኞች ብዙ ምጽዋት የሚሰጥ አንድ ባለጸጋ ሰው አገኘ። ይህ ድሃ ጌታዬ እዘንልኝ መቶ ወቄት ወርቅ ስጠኝ ሔጄ እነግድበት ራሴን እረዳበት ዘንድ ገንዘብህንም ከነወለዱ እከፍለሃለሁ አለው። ባለጸጋውም ድሃውን እኔ አላውቅህም ይህም ባይሆን ዛሬ ከዚህ ሀገር የሚዋስህ አንድ ሰው አምጣ። በኔና በአንተ መካከል ፀብ እንዳይሆን ገንዘቤን የሚመልስልኝ ዋስ ስጠኝ አለው። ይህም ድሃ ባለጸጋውን እኔ ድጋ ነኝና የሚዋሰኝ አላገኝም። አሁንም ፈቃድህ ከሆነ ከራራህልኝም ተነስተህ እኔም አንተም ሁለታችንም የመላእክት አለቃ ወደ ሚሆነ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እንሒድ እሱ አለቃዬ ነውና ይዋሰኛል አለው። ይህም ባለጸጋ አንተስ በቅዱስ ሚካኤል የምታምን ከሆነ እኔም አምንበታለሁና ተነሥ እንሒድ አለው። ከዚህ በኋላ ሁለቱም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ባለበት አንድነት ቆሙ። ይህም ደሃ የመላእክት አለቃ ጌታዬ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ስለዚህ ባለጻጋ አላመነኝምና አንተ ጌታዬ ተዋሰኝ አለው። ከዛሬ ጀምሮ በዓልህ እስከሚከበርበት ሰኔ አሥራ ሁለት ቀን ድረስ ለባለገንዘቡ ወርቁን እመልሳለሁ አለው። ይህም ባለጸጋ ነገርክን ሰማሁ ተነስ እንሂድ ልስጥህ አለው። ይህ ነገር ለባለጸጋው ድንቅ ሆኖበታልና። ከዚህ በኋላ ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ሁለቱም አንድነት ወደባለጸጋው ቤት ሔዱ። ባለጸጋውም መቶ ወቄት ወርቅ ሰጠው። ድሃውም የተሰጠውን ወቄት ወርቅ ይዞ ደስ እያለው ወደቤቱ ተመለሰ ከዚህም በኋላ ወደሮም አገር ሔደ በዚያ ወርቅም ነገደና አተረፈ። ከዚህ በኋላ ቀጠሮው የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል በዓል የሚሆንበት ዕለት ሰኔ አሥራ ሁለት ቀን እንደደረሰና ወደ ሀገሩ ሊመለስ እንዳልቻለ በአወቀ ጊዜ ጽኑ ኀዘን አዘነ። ተቆረቀረ። በልቡናውም አስቦ እንዲህ አለ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ዋስ ያደረግሁበት ጊዜው ደረሰ ዛሬ መድረስ አልተቻለኝም ምን ላድርግ አለ። ያን ጊዜም የቅዱስ ሚካኤልን ተራዳኢነት የፈጣሪውንም ከሃሊነት አሰበ።ከዚህ በኋላ እጁን ወደ ሰማይ ዘርግቶ አንገቱን ወደ ላይ አቅንቶ ጸለየ። በፍጹም ልቡና በፀና ሃይማኖት ታምኖ ለባለ ዕዳው ከአምሳ ትርፍ ጋራ መቶውን ወቄት ወርቅ ይዞ በከረጢት ቋጥሮ በከረጢቱም ውስጥ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ስምና የባለጸጋውን ስም ከነሱም ጋር የእሱን ስም ጻፈ። ከዚህ በኋላ ተነስቶ ወደ እንጥረኛ ሔዶ አንጥረኛውን የእርሳስ ሣጥን ሥራልኝ አለው። የእርሳስ ሣጥን ሠራለት። ከዚህ በኋላ ይህን ከረጢት ወስዶ ከውስጡ ጨምሮ ዘጋው። ከዚህ በኋላ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል በዓል ዋዜማ ቀን ወደ ወንዝ ሔደ ከባሕር ዳርም ቆሞ አቡነ ዘበሰማያት ደገመ እግዚአብሔርን ፈጽሞ አመሰገነ። በፍጹም ሃይማኖቱም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እነደተዋስከኝ ባለጠጋውና እኔ የተቃጠርንበት የበዓልህ ቀን ዛሬ እንደሆነ እኔም ከሩቅ አገር እንዳለሁ ዛሬም እስክንድርያ መድረስ እንዳይቻለኝ አንተ ታውቃለህ አሁንም የባለጠጋውን ገንዘብ ከነወለዱ ለአንተ ሰጥቼሃለሁ ለባለ ዕዳዬ መልስልኝ ብሎ ጸለየ ጸሎቱንም በጨረሰ ጊዜ ሣጥኑን ከነ መክፈቻው ወደ ባሕር ወረወረው ያን ጊዜ ጊዜውን ታላቅ ዓሣ ወጥቶ ሣጥኑን ተቀብሎ ዋጠው። ከዚህ በኋላ ያ ዓሣ በአንዲት ሌሊት የስድስት ወር ከስድስት ቀን ጎዳና ተጉዞ በነጋው ፀሐይ በወጣ ጊዜ ከእስክንድርያ ባሕር ወደብ ደረሰ። በዚች ቀን ያ ባለጸጋ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል በዓል ዓሣ ሊያሠግሩ ሔደው ከባሕር ላይ መረባቸውን ይጥሉ ዘንድ ብላቴኖቹን አዘዘ። ያ ዓሣ ተያዘና ወደ ባለ ጸጋው ወሰዱት ባለጠጋውም ባየው ጊዜ ደስ አለው ታላቅ ነበርና። ባለጠጋውም ብላቴኖችን ይህን ዓሣ ለበዓሉ ቅዱስ ሚካኤል አመጣልኝ አላቸው። ብላቴኖችን ያን ዓሣ ጥቡት ብሎ አዘዛቸው ሆዱንም በቀደዱት ጊዜ በዓሣው ሆድ ውስጥ ይህን የዋጠውን ሣጥን አገኙት። ይህንን ብሎት እጁን ዘርግቶ ሁለንተናውን ዳስሶ እግዚአብሔር ፈጽሞ አድኖሃልና ተነስተህ ሒድ አለው። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ቀንቶ በእግሩ ተነስቶ ሔደ። የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ፈጣሪ እግዚአብሔርን እያመሰገነ።ከደዌው ስለ ዳነ ፈጽሞ ደስ አለው። በፍጹም ደስታ ቃል እያመሰገነ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ሰገደ። https://s.imoim.net/zlwusE አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት አሥራ ሁለት ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል በዓል መታሰቢያ ነው። በዚች ቀን ክብር ምስጋና ይግባውና እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን የረዓይት ወገን ወደሚሆን ወደ ሶምሶን ልኮታልና።....... ሊገድሉት የፈለጉትን የፍልስጥኤምን ሰዎች ድል እስኪያደርጋቸው ድረስ ረድቶታልና። በእነሱ ላይ እግዚአብሔር ኃይል ሰጥቶት አጠፋቸው ከእነሱ በአንዲት ቀን በአህያ መንጋጋ ሺህ ሰው ገደለ። ውሃ ጠምቶት ሊሞት በደረሰ ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ታይቶ አፀናው ከአህያ መንጋጋ አጥንትም ውሃ አወጣለት ጠጥቶም ከውሃ ጥም ዳነ። https://s.imoim.net/zlwusE የፍልስጥኤም ሰዎች ድል በሆኑ ጊዜ ከሚስቱ ጋር ተማክረው ዓይኑን አጥፍተው ወደ ጣኦታቸው ቤት ወሰዱት። የእግዚአብሔር መልእክተኛ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ታየው ተነጋገረው ኃይልንም ሰጠውና ሁሉንም አጠፋቸው ስለዚህ ነገር የቤተ ክርስቲያን መምህራን በየወሩ በአሥራ ሁለት ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ። አዝዘውናል። ልመናው ከእኛ ከሀገራችን ከኢትዮጵያ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን። #ዘወረደ #አቢይጾም #የኪዳንጸሎት #የጾምጉባኤ #ኦርቶዶክስተዋህዶ #ኢትዮጵ #GreatLent #Zewerede #OrthodoxTewahedo #LentPrayer #EthiopianOrthodox #SpiritualConference #ዓቢይጾም #ዘወረደ #ጸሎትኪዳን #ተዋህዶ #SoomaGuddaa #Zewerede #ክዳንዕ https://s.imoim.net/zlwusE #Ortodoxii #AbiyTsom #Zewerede https://s.imoim.net/zlwusE