У нас вы можете посмотреть бесплатно የጥር 18 ሥንክሳር или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ስንክሳር ዘወርኀ ጥር 18 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን ። ቅዱስ ያዕቆብ ዘንፅቢን (ከ፫፲፰ቱ) በዚችም ዕለት በገድል የተጸመደ የከበረ አባት ለቅዱስ ኤፍሬምም መምህሩ የሆነ የሀገረ ንጽቢን ኤጲስቆጶስ አባ ያዕቆብ አረፈ ። ይህም ቅዱስ ተወልዶ ያደገው በንጽቢን ከተማ ነው እርሱ ግን ሶርያዊ ነው ከታናሽነቱም የምንኵስና ልብስ መልበስን መረጠ ከጠጉር የተሠራ ማቅንም ለበሰ በጾሞ በጸሎት ተወስኖ በቀን በሌሊት በበጋ ሐሩርበክረምት ቁር የሚጋደል ሆነ ያንንም ማቅ ከቶ ከሥጋው ላይ አያወጣውም ነበር ምግቡም ቅጠላቅጠል ነው የሚጠጣውም የዝናብ ውኃ ብቻ ነው ስለዚህ ሥጋው ብሩህ ሆነ ነፍሱም እጅግ በራች ። እግዚአብሔርም ሀብተ ትንቢትን ድንቆች ተአምራቶችንም የመስራት ጸጋን ሰጠው ለሰዎችም ከመሆኑ በፊት የሚሆነውን ይነግራቸውና እንዲሁም ይሆናል ። ተአምራቱም እጅግ ብዙ ነው በአንዲትም ቀን ሴቶች በውኃ ምንጭ ላይያለማፈር ሲጫወቱና ሲሣለቁ አያቸው የውኃውንም ምንጭ አደረቀ የራሳቸውንም ጠጉር ነጭ ሽበትን አደረገ በተጸጸቱና የውኃውን ምንጭእንዲመልስላቸው እየሰገዱ በለመኑት ጊዜ የውኃቸውን ምንጭመለሰላቸው እንዳይታበዩም ይገሠጹ ዘንድ የራሳቸውን ጠጉር ነጭእንደሆነ ተወው ። በአንዲት ዕለትም በጎዳና አልፎ ሲሔድ አንዱን ሰው እንደሞተ ሰው አስተኝተው ሰዎችን አገኛቸው መገነዣ ልብስም ይሰጣቸው ዘንድ ቅዱሱን ለመኑት እርሱ ግን በጸሎቱ ሰውዬውን ምውት አደረገው ስዎችም ወደርሱ በተሰበሰቡ ጊዜ ሙቶ አገኙት ተጸጽተውም ሁለተኛ ያድንላቸው ዘንድ ለመኑት አዳነላቸውም ። ትሩፋቱና ደግነቱም በተሰማ ጊዜ መርጠው በሀገር ንጽቢን ላይኤጲስቆጶስነት ሾሙት የክብር ባለቤት የክርስቶስን መንጋዎች ከአርዮሳውያን ተኵላዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ ። ንጉሥ ቁስጠንጢኖስም የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱን የከበሩ አባቶች በኒቅያ ከተማ በሰበሰባቸው ጊዜ ይህ አባት አብሮ አለ ከእርሳቸውም ጋርአርዮስን አውግዞ ከክርስቲያን አንድነት ለየው የቤተ ክርስቲያንንም ሥርዓትና በሁሉ ምእመናን ዘንድ የታወቀች የሃይማኖት ጸሎትን ሠራ ። ንጉሥ ቁስጠንጢኖስም በደረሰ ጊዜ የሞተውን ሰው በጉባኤው ውስጥ አስነሥቷል ። የፋርስ ንጉሥም መጥቶ ሀገረ ንጽቢንን በከበባት ጊዜ ይህ ቅዱስ ያዕቆብ የጭጋግ ደመና በሠራዊቱ ላይ አመጣ ትንኞችም ፈረሶቻቸውንና ጎበዛዝቶችን ነደፏቸው ፈረሶችም ማሠሪያቸውን ቆርጠው ፈረጠጡ የፋርስ ንጉሥም አይቶ ታላቅ ፍርሀትን ፈራ ተነሥቶም ሸሽቶ ወደኋላው ተመለስ ። ነፍሱን የመንጋዎቹንም ነፍስ ጽድልት ብርህት አድርጎ ገድሉን በፈጸመ ጊዜ አረፈ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት ከአራት ቀኖች በኋላ ጌታችን ከመቃብር ያስነሣው የአልዓዛር እኅቶች የማርያና የማርታ መታሰቢያቸው ሆነ በረከታቸውም ከእኛ ጋር ይኑር ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አሜን ። ጥር ፲፰ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1. የቅዱስ ጊዮርጊስ የሰማዕታት ክበብ የአፅሙ ማውጣት ፪.ቅዱሳት ደናግል ማርያ እና ማርታ ከ፫፮ቱ ቅዱሳት አንስት ፫.ቅዱስ ያዕቆብ ዘንፅቢን ከ፫፲፰ቱ ፬.ቅዱስ ባኮስ ኢትዮዽያዊ አቤላክ / አቤሜሌክ ወርኀዊ በዓላት ፩.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ ፪.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ፫.አባ አኖሬዎስ ፬.ማር ያዕቆብ ግብፃዊ @OrtodoxTewahedo21 @እናታችንማርያምሆይእንወድ @Fewus_Menfesawi_Aba_Gebrekidan