У нас вы можете посмотреть бесплатно እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ ወደ መስኖ አምባ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ ወደ መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ-ገብረ-መንፈስ ቅዱስ ፨ በደቡብ ወሎ አገረ ስብከት በወገልጤና ከተማ የሚገኝ በአፄ ንብለ ድንግል ዘመነ መንግስት መስቀል አውጭ (ዋሌ)ዋሻ እየተባለ በሚጠራው ቆላማ ቦታ አባ ሔርሜ በሚባሉ ባህታዊ ለ100 ዓመት ያክል ሲገልገል የቆየ መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፨ ግራኝ አህመድ በዋድላ ደላንታ አውራጃ በረካታ አብያተ ቤተክርስቲያንን ሊያቃጥል አስቦ በተንቀሳቀሰበት ወቅት ከቃጠሎና ከወረራ ለማዳን አቦ ዋሻ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በመሠወር ለብዙ ጊዜ ሲገለገል የቆየ መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፨1888 ዓ.ም አሁን ላይ ህንፃ ቤተ-ክርስቲያንኑ በሚገኝበት ቦታ በእንጨትና በሳር ክዳን በደጃች አበጋዝ አስተባባሪነት ተሰርቶ 1961ዓ.ም የሳር ክዳኑ ተነስቶ የቆርቆሮ እድሳት ተደርጎለት እስከአሁኑ ስዓት እያገለገለ የሚገኝ በዚህ ቤተክርስቲያን እጥር ግቢ ውስጥም በደጃች አበጋዝ የተተከሉ 64 ጥዶች 4 ወይራዎች የሚገኙበት መስኖ አምባ መካነ -ህይዎት አቡነ -ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፨ የሆድ ህመም የነበረባቸውና በእብድ ውሻ የተለከፉ ሰዎችም ፀበሉን ጠጥተው መስቀሉን ታሽተው በገድሉ የተፈወሱበት። መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፨ከታሪክ እንደምንረዳው አባቶች በመሐሌት ቁመው በአንድ እጃቸው ከበሮ በሌላኛው እጃቸው ጸናጽን ይዘው "ሰው አፍራ እያሉ" በጽናት አገልግለው ለትውልድ ያስረከቡት ጥንታዊና ታሪካዊ ቤተክርስቲያን ታዳ ይህን ህንጻ ቤተክርስቲያን በአድስ መልክ መሰራት ከተጀመረ ቀናቶች ወራቶች ዓመታት ተቆጥርው አሁን ከደረሰበት ደረጃ ደርሷል። እነሆ ህንጻ ቤተክርሲቲያኑ ሰርቶ ለማጠናቀቅ የደብሩ ህንጻ ኮሜቴና ሰበካ ጉባኤ የጻድቁ አባታችን ዓመታዊ በዓልን ምክኒያት በማድረግ ልዩ የበረከት ስራ አዘጋጅቷል። የበረከት ስራው መጋቢት 1 ቀን ይጀመራል እስከ መጋቢት 15 ቀን ድረስ ይቀጥላል። መጋቢት 1 ቀን የሚሰጡ እጆች ሁሉ ወደ መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መዘርጋት የሚጀምሩበት ቀን መጋቢት 1 ቀን የሚሰጡ ደግ ልቦች ሁሉ መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ መድረስ የሚጀምሩበት ቀን እኛስ? እጆቻች ወደ መስኖ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለመዘርጋት ተዘጋጅተን ይሆን? ልባች በመንፈስ ወደ መስኖ አምባ መካነ ሕይወት አቡነ መንፈስ ለመለገስ ይደርስ ይሆን? ከበረከቱ እንሳተፍ የበረከት ጥሪውን ላልደረሱ እናዳር ሽር እናድርግ የቴሌግራም ግሩፑን እንቀላቀል የቴሌግራም ግሩፑን ለመቀላቀል ሊንኩን ይጫኑ የመስኖ አምባ መካነ ህይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ህንጻ ኮሚቴ እና ሰበካ ጉባኤ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0914601571/0913782107 ይደውሉ https://t.me/+JIOWNCaz1LlkNDY0