У нас вы можете посмотреть бесплатно የፍቅር ሃያልነትን//የትዳርን ትልቅነት//የእግዘብሔርን ተዓምር//በእዉነተኛ ታሪክ እንመልከት или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
@donkeytube.eshetumelese @abelbirhanu1 @21media27 #trending #cute couple #besintu_sitcom #besintu #life #love #love-life #husbandwife #coupleprank #prank #funny #habeshaprank Ye beata -፫-:like ስታረጉ ብዙ ሰዉ ጋር ይደርሳል💡 ሄራንን ያወክዋት ድሮ ልጅ እያለን ሰንበት ትምርትቤት ነበር። ስናድግም ከሰንበት ትምርትቤታችን ብዙም ስላልራቅን ቅርርባችን እጅግግ ቀጠለ በጣም ስለተቀራረብ ወደ ፍቅር መቀየር አልከበደንም የሁሉ ሰው አይን ውስጥ ገባን አብረን ማስቀደስ አብረን መቁረብ አብረን ገዳም መሄድን ተያያዝነው ቀድሼ ሳቆርባት የሚሰማኝ ስሜት ልዩ ነው የእግዚያብሔር ስጦታዬ ናት...........በ26 አመታችን ለመጋባት ወሰንን ከብዙ ውጣ ውረድ በኃላ የሽምግናውየሰርግ ወከባው አሁንም አይኔ ላይ ነው። ሰርግ ግን ደስ ሲል በእግዚአብሔር ፊት ቃል ኪዳን መግባት ዘመድ አዝማድ ፊት የእግዚአብሔር ሽልማቴ የሆነችውን እስዋን ለህዝብ ማሳየት የሚደገም ቢሆን ሁሌ ነበር የማደርገው። የተጋባናው መጋቢት 11 ነበር............."እመቤታችን ባንቺ ምልጃ ባንቺ ምልጃ ድንግል ማርያም ባንቺ ምልጃ...........' እየተዘመረ እውነትም በእስዋ አማላጅነት መድኂኒት አለም ታምር መስራቱ የእኛ ህይወት ማሳያ ነው....... '' ወይ አይደለሽ ጊሸን ወይ አክሱም ፂዬን እንዴት አድርጎ መረጠሽ ካህን" ተብላ ውብ ቀን ነበር። program አልቆ ወደቤት ስንሄድ የመኪናው የኃላ መቀመጫ ላይ ልክ ንጉስ እና ንግስት መስለን ዞሬ ወደ እስዋ አየው እምባዬ መጣ የልጅነት ፍቅሬ የዘላለም ህይወቴ የኔ.......የኔ ብቻ መሆንዋን ሳስብ እግዚአብሄርን አመሰገንኩት በልቤ ሌላ ቃል ኪዳን አሰርኩላት ሁሌም እንዲህ ውብ ሆና እንደምትኖር ፍቅሬን ለደቂቃ እንደማልቀንስባት ሌላ Beata ለኔ: ወር አለፈ ቤት ውስጥ ድሪያ ለብሳ ፀጉረርዋን ወደኃላ አሲዛ ሳያት ይበልጥ ታሳዝነኛለች ትክከክ ብዬ ሳያት ሁልጊዜ "ምነው ቆንጆ አይተህ አታውቅም" ብላ ትስቃለች በርግጥ አዎ አይቼ አላውቅም አንቺን ብቻ ነው ከልጅነት እስከ አሁን ያየሁት አንቺን ብቻ ሀ ብዬ ጉርምስና ስጀምር ልቤ የከጀለው አንቺን ነው መኖርን የጀመርኩት ህይወት የገባችኝ ባንቺ ነው የእኔ አበባ ልላት እፈልግና አብሮኝ የኖረው አይናፋርነቴ ይይዘኛል እንኳን የኔ ሆንሽልኝ ። በተጋባን በሶስተኛው ወር የሆነ ቀን ሌላት ላይ የሆነ የወደቀ ነገር ተሰማኝ ብርድልብሱን ከላዬ አራግፌ ድምፁ ወደተሰማበት ከነፍኩ ሄራን ነበረች "እናት ምን ሆንሺብኝ" "እኔንጃ ልነሳ ስል እግሬ ከዳኝ" እንሰቼ አልጋ ላይ አስቀመኳት ረጥባለች ሽንትዋ አምልጥዎት እንደሆነ አይንዋ እምባ አቅርሮ ነገረችኝ የኔ ምስኪን ተሳቃ እኮ ነው ቆይ ባል ይታፈራል? ተነስተን ሶፋ ላይ ተኛን በነጋታው ስራ ለመሄድ ስነሳ ቀድማኝ ነቅታ ነበር "አባቴ እግሬ እምቢ አለኝ አለች" "አትቀልጂ ተነሺ" "ማርያምን እግሬ አልታዘዝ አለኝ" እያለቀሰች ነበር ማርያምን እግሬ አልታዘዝ አለኝ" እያለቀሰች ነበር አንስቼ ለማቆም ሞከርኩ ልትወድቅ ስትል አቀፍክዋት ደንግጠን ወደ ሆስፒታል ሮጥን ቆይ ከፈረንሳይ ስድስት ኪሎ እንዲህ ይርቃል? ረጅምምም ምርመራ አደረጉላት ከወገብዋ በታች pralize ሆናለች ሽንትዋንም ምንም መቆጣጠር እንደማትችል መልአከ ሞት የመሰለ ሀኪም አረዳኝ እየቆየ ወደ ላይ ከፍ ሊል እንደሚችል እና ሙሉ ለሙሉ ልትንቀሳቀስ ልትችል እንደማትችል አቀርቅሮ ነገረኝ ለልቤ ትልቅ ሰይፍ የገባበት ይመስል አመመኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ ጌታ ሆይ በእኔ ሀጢያት ለምን እስዋን ለምን ሚስኪንዋን በናትህ እኔን ቅጣኝ እስዋን ማርልኝ ብዬ ተደፍቼ አነባሁ ከቀን ወደ ቀን ሁኔታው እየከፋ መጣ የአዋቂ ዳይፐር ትልቁ ወጪአችን ሆነ ሙሉ ሰውነትዋም አልሰራ አለ ብዙዙዙ ግዜ ከስራ ስቀር መስሪያቤቴ አባረረኝ እናትዋ የአስም በሽተኛ ናቸው እኛ ጋር በመጡ ቁጥር ይታመማሉ አባትዋ ደሞ ሳይነስ አለባቸው ሁለቱም መምጣት አይችሉም ቤተሰብ ዘመድ ራቀን.......ዳይፐር ስቀይርላት ትሳቀቃለች ታለቅሳለች ላፅናናት ስል ስቅስቅ ብላ ስለምታለቅስ ማደርገው ይጠፋኛል። የሆነ ቀን እናትዋ ቤት መጡ እያለቀሱ እንዲህ አሉ " ልጄ ለምን አትፈታትም እኛ በቃ እንደምናደርግ እናደርጋለን ወይ ሰው እንቀጥራለን" እያሉ ንግግራቸው አቋርጬ "እማማ በቃዎት ሚስት ናት እኮ እግዚኣብሄር ፊት ቃል የገባሁባት ታመመች ብዬ ጥያት ብሔድ እግዜርስ ምን ይለኛል እወዳታለሂ አልሰለቸቺኝም አትሰለቸኝም......መስቀሌ ናት እኮ እማማ.......አሁንም አትሰለቸኝም......መስቀሌ ናት እኮ እማማ.......አሁንም በጣም ነው የማፈቅራት አልከበደችኝም" ብዬ ከየት እንደመጣ የማላውቀው እምባዬ ዝርግፍ አለ ስናወራ ሰምታን ነበር እና ሄራንዬ ራስዋን በትራስ ሽፍና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች አቅፌአት አለቀስኩ የቤተሰቦችዋ ፍታት ጉትጎታ ሲበዛ አወራዋት "446" "ኤ" "ለምን ጸበል አንህድም?'' "የዚህ ስቃይ አልበቃ ብሎህ ሌላ ስቃይ?'' "እንደዛ አትበይ ተሰቃየሁ አልኩ?" "ቢሆንም እኔ ተሳቀቅሁኝ" "እንዳታለቅሺ ይቺን ውብ አይንሽን እንዳታለቅሺበት ደግሞ ዛሬ እንዴት ነው ምታምሪው የኔ ሚስት ባትሆኚ ኖሮ" "የኔ ጌታ ታሳዝነኛለህ እሸታለሁ እኮ" "እሱን ተይውና ይዜሽ ልሂድ እ እናት እ እ እ እ" "እ.......ሺ ሸክም እንዳልሆንብህብዬ ነው እኮ" "ሁለተኛ እንዲህ እንዳትይ ለኔ መቼም ሸክም ሆነሽብኝ አታውቂም የኔ ፍቅር" እጣ አወጣን ፃድቃኔ ማርያም "አይሽ ፍቅር እናቴ ማርያም ታምርዋን ልታሳየን ነው እኮ" ገንዘብ ስላልነበረን መኪናዬን ሽጬ ለማንም ሳንናገር ተነስተን ፃድቃኔ ማርያም ሄድን እግዚአብሔር ምስክሬ ነው አንድ ቀን ሰልችቶኝ አያውቅም የእስዋን ዳይፐር መቀየር እስዋን ማጠብ እስዋ ግን ተሳቃ አለቀችብኝ። አንዳንዴ ፍታኝ እና ሂድ ትለኛለች ተደብቄ ከማልቀስ ውጪ ምንም ምርጫ አልነበረኝም አንዳንዴ አጥቤአት እንደጨረስኩ ውጣልኝኝ ብላ ትቆጣለች መሄጃ ስለሌለኝ ወጥቼ በርላይ ሁሉ አድራለው ትንሽ ተኝታ ታድራለች ስትተኛ ደግሞ ስታሳዝን በዲቁናዬ የሚያውቀኝ አንድ መልካም ሰው አገኘው አዛ እንዳገለግል አናገረልኝ ለእኔ መደበቂያ ሆነኝ መንበሩ ስር ድፍት እያልኩ አለቅሳለው ማርልኝ ጌታዬ እያልኩ እንዲህ እንዲህ እያለ የጽጌ ጾም ገባ እንደለመድኩት እስዋን አጥቤ እራት አብልቼ ስትተኛ ማህሌት ልቆም ወደ ቤተ መቅደስ በባትሪዬ እየተመራው ሄድኩ አቤት ሲያምር ማህሌቱ ልክ አክሊለ ጽጌ ማርያም ብለን ወረብ ስንጀምር ጩኸት ሰማው ሄራን ሄራን የሚል ልቤን ልተፋው ደረሰ በጣም ይመታል መዞር ፈራው የሞት ሞቴን ስዞር. .ሚስቴ ከአጠገቤ ቆማለች እምባ አንቆዋት "ዳንኩ እኮ" "ይቅር ተባልኩ እኮ' እምባፊትዋን ሞልቶ ተረፍኩ አለችኝ ቤተ መቅደሱን በእልልታ ተሞላ.......ከቤተመቅደስ ይዛት ወጥቼ አቅፌአት አለቀስኩ ለቅቄአት እመቤቴ ምስለ አድኖ ፊት ተንበረከኩ እምባ ዝም ብሎ ይፈሳል አንዳንዴ ግን እምባ በአፍ ያልተነገረ ፀሎት ነው ምስጋናም ጭምር....... ከሳምንት በኃላ እንዴት መቆም እንደቻለች ጠየክዋት በህልምዋ