У нас вы можете посмотреть бесплатно ከቀጥታ ከየካ ሚካኤል | ላሊበላ 24 - lalibela 24 | или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
በመስቀል አደባባይ ለሚካሄደው "የአእላፋት ዝማሬ" ዝግ የሚሆኑ መንገዶች አዲስ አበባ ታህሳስ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ነገ ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በገና በዓል ዋዜማ በመስቀል አደባባይ የሚካሄደውን ታላቅ የአእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር ተከትሎ፣ የትራፊክ መጨናነቅን ለመከላከል ሲባል በርካታ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። ከዛሬ (ታህሳስ 27) ምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ፡ በሚዘጉ መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ ነው። ከነገ (ታህሳስ 28) ቀን 6:00 ሰዓት ጀምሮ፡ መርሐ ግብሩ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ሙሉ በሙሉ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ መሠረት የሚከተሉት መንገዶች ዝግ ይሆናሉ፦ 1.ከመገናኛ መስመር፦ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ 2.ከቦሌ/ጌቱ ኮሜርሻል መስመር፦ ኦሎምፒያ ወይም ደንበል አካባቢ 3. ከመስቀል ፍላወር መስመር፦ ጋዜቦ አደባባይ 4. ከጎተራ መስመር፦ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ፤ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ 5.ከጎፋ (አዲሱ መንገድ)፦ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ-ክርስቲያን መስቀለኛ 6. ከሜክሲኮ መስመር፦ ለገሃር መብራት 7. ከአምባሳደር መስመር፦ ሐራምቤ መብራት 8. ከአራት ኪሎ መስመር፦ ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት የጥቆማ ስልክ መስመሮች ማንኛውም የፀጥታ ስጋት ወይም አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ ህብረተሰቡ በሚከተሉት ስልኮች እንዲያሳውቅ ተጠይቋል፦ በነፃ መስመር፦ 987፣ 991 ወይም 816 በመደበኛ ስልክ፦ 011-126-43-59 / 011-552-63-02 በመተግበሪያ፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ መተግበሪያ (EFPApp) ፖሊስ ለፕሮግራሙ ሰላማዊ መጠናቀቅ የከተማው ነዋሪና የታዳሚዎች ትብብር ወሳኝ መሆኑን ገልጿል።