У нас вы можете посмотреть бесплатно ጸሎተ ፍትሐት፣ በዶርማገን ( Dormagen ) በግፍ ለተገደለው ታዳጊ ልጃችን ዮሴፍ ( ገ/እግዚአብሔር ) የከተማው ተጠሪ በተገኙበት የተደረገ ጸሎተ ፍትሐት። или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ጸሎተ ፍትሐት፣ በዶርማገን ( Dormagen ) በግፍ ለተገደለው ታዳጊ ልጃችን ወንድማችን ዮሴፍ ( ገ/እግዚአብሔር ) የበዶርማገን ( Dormagen ) ከተማ Bürgermeister ተጠሪ sozialintegration አብሮ የመኖር ኃላፊ የሆኑት በተገኙበት የተደረገ ጸሎተ ፍትሐት። ብላቴና ዮሴፍ መልአኩ 2004 - 2018 /2012-2026/ ጥር 4 ቀን 2004 ዓ.ም የተወለደው ብላቴና ዮሴፍ መልአኩ ወደዚች ዓለም በመጣ በ14 ዓመቱ ጥር 20 ቀን 2018 ዓ.ም አረፈ። የ40 ቀን መታሰቢያና የጸሎተ ፍትሐት መርሐ ግብር በርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ኮሎኝ-ቦን ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን። ድንገት በሰው እጅ ሕይወቱ የተቀጠፈው የ14 ዓመቱ ዮሴፍ መልአኩ የ40 ቀን መታሰቢያና ጸሎተ ፍትሐት በርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ኮሎኝ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የካቲት 29 ቀን 2018 /08.03.2026/ ተፈጽሟል። በ ግብጽ ምድር ተወልዶ በአራት ዓመቱ ከእናቱ ጋር በአደገኛው የስደት ጉዞ በሊቢያ በርሃና በመካከለኛው ባሕር አድርጎ ወደ ጀርመን ከመጣ ወዲህ ላለፉት ስምንት ዓመታት በሚገርም ፍጥነት ከሚኖርበት ኅብረተሰብ ጋር የተላመደና በተለየያዩ እንቅስቃሴዎች በንቃት የሚሳተፍ ልጅ እንደነበር በቅርብ የሚያውቁት ሁሉ ይናገራሉ። የልጇ ሞት መንስኤ ግራ ያጋባት እናቱ ወ/ሮ ሊሊ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከጎኗ ሆነው ያጽናኗትን ጎረቤቶቿን፣ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያንን እንዲሁም አባታችን ሊቀካህናት ዶ/ር መርዓዊ ተበጀን ከልብ አመስግናለች። ልጄን አንዴ አጥቼዋለሁ፣ ወደ አምላኩም ሄዷል፣ ያለቸው ይህች እናት፣ ወንጀሉን በመፈፀም የረጠረጠረው የ12 ዓመቱ ጀርመናዊ ድርጊቱን ለምን እንደፈፀመው እንዲገልፅልኝ እፈልጋለሁ ነው የምትለው። ከዚያ ውጪ አሁን ምንም አይናገርም የተባለው በድርጊቱ ፈፃሚነት የተጠረጠረው አዳጊ ልጅ ላይ የሚወሰደው የትኛውም ቅጣት ልጄን አይመልስልኝም ባይ ናት። ሌሎች ወላጆችን " ከእኔ ተማሩ: በእኔ ይብቃ" ስትል ምክሯን ለግሳለች። ከ40 ዓመት በላይ ጀርመን ሀገር በኖሩባቸው ጊዜያት በእንዲህ ያለ አሟሟት ሕይወቱ ያለፈ ወገን እንዳላጋጠማቸው የተናገሩት ሊቀካህናት ዶክተር መርዓዊ ተበጀ አጋጣሚው ለወላጅ እናቱና ለቤተሰቦቹ ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ያሳዘነና ያስደነገጠ: እንደ ወላጅ መሪር ኃዘን መሆኑን ገልጸው፣ "ማጽናኛ ቃል አላገኘሁም፣ እግዚአብሔር አምላክ አጽናኝ የሆነውን ቅዱስ መንፈስ እንዲልክላት የዘወትር ጸሎታችን ነው" ብለዋል። የዮሴፍ አሟሟት እስካሁን የኖረበትን ከተማና አካባቢ ነዋሪዎች ግራ እንዳጋባ መሆኑን በ40 ቀን የመታሰቢያ ሥርዓቱ ላይ የዶርማገን ከተማ ከንቲባን በመወከል የተገኙት የከተማዋ የኢንቲግራሲዮንና የማኅበራዊ ኑሮ ዘርፍ ኃላፊ ሄር ሌቨሬንዝ (Herr Lewerenz) ተናግራዋል። በምዕራብ ጀርመን ኖርድ ራየን ፌደራል ግዛት የዶርማገን ከተማ ስደተኞች ከሀገሬው ቋንቋ፣ ባህልና የአኗኗር ዘይቤ ጋር ተላምደው ለመኖር የሚያደርጉትን ጥረት የሚያግዘው ኢንተግራሲዮንና የማኅበራዊ ኑሮ ዘርፍ ተጠሪው ባደረጉረጉት አጭር የማጽናኛ ንግግርም በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የዮሴፍን ቤተሰቦች ችላ ማለት እንደማይገባና ከጎናቸው መቆም እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። ብላቴና ዮሴፍ መልአኩ ከአረፈበት ቀን አንስቶ የማኅበረ ክርሰቲያኑ ትብብር እጅግ የሚያስመሰግን ነበር። በተለይም ኃዘንሽ ኃዘኔ" በሚል ስያሜ የተሰባሰቡት እናቶችና እኅቶች በጸሎተ ፍትሐቱ ዕለት ያቀረቡት መስተንግዶ እጅግ የተዋጣለት ነበር። የደብሩ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤም ጥልቅ ምስጋናውን አቅርቧል። በዕለቱ የቀረበው ጸሎተ ቅዳሴም ከእንባ ጋር ነበር። የዮሴፍ ድንገተኛ አሟሟት አሳዛኝ ከመሆኑ ሌላ ለሌሎች ወላጆች የማሰጠንቀቂያ ደውል እንደሆነ ነው ብዙዎች ያመለከቱት። የድርጊቱ ፈጻሚ ማንም ይሁን ማን የብላቴናው የዮሴፍ መልአኩ ደም እንደ አቤል ደም ወደ እግዚአብሔር ይጮሀል እግዚአብሔርም ዝም አይልም የንጹሐንን ደም ይበቀላል የሟቹን ነፍስ ይማር ነፍሱንም በአፀደ ገነት ያሳርፍልን ከዳግም ኃዘን ይሰውረን።