У нас вы можете посмотреть бесплатно Kefale Alemu on Debir Zena Markos Sacred Church & Its Thrilling Surrounding Environment in Ethiopia или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
This video presents the sacred Debir Zena Markos Church and the thrilling surrounding environment in Moret & Jiru Awraja (North Showa), Ethiopia. Debre Bisrat Debir Zena Markos Church and Monestary is found about 10 Kilometres away from the historic town of Enewari. Acts of Saint Abune Zena Markos ቅዱስ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ ሃገራቸው ሸዋ ዉስጥ ዞረሬ /ጽላልሽ/ ነው። አባታቸው ካህን ዮሃንስ የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የአቡነ ጸጋዘአብ ወንድም ነው። እናታቸው ዲቦራ (ማርያም ዘመዳ) ትባላለች። የአቡነ ቀዎስጦስ እህት ናት። በብስቃረ ማርቆስ ወንጌላዊ ህዳር ፳፬ /24/ ተወልዷል። አርባ ቀን ሲሞላቸው ሊያስጠምቋቸው ቤተ ክርስቲያን ወሰዷቸው። ጸሎተ ጥምቀቱ ደርሶ ከውሃ ውስጥ ሲከቷቸው ቆመው እሰግ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብለው 3 ጊዜ ሰግደዋል። ውሃው ፈላ አጥማቂው ቄስ የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የአቡነ ጸጋዘአብ ወንድም ካህኑ እንድርያስ ነበር። እድሜው 72 ዓመት ስለነበር በሕፃኑ ድርጊት ፈርቶ ወደ ቤተ መቅደስ ሮጠ። ቅዱስ ሩፋኤ ከፍርሃቱ አጽናንቶት ከማየ ጸሎቱ ራሱን እንዲቀባ ነግሮት በራ የነበረ ራሱ ጸጉር በቅሎለታል።አቡነ ዜና ማርቆስ 5 ዓመት ሲሞላቸው ወላጆቻቸው ለመምህር ሰጧቸው። በ 3 ዓመት ብሉይንና ሐዲስ አጥንተው በ8 ዓመታቸው ከቅዱስ ቄርሎስ ድቁና ተቀብለው ሲመጡ ሽፍቶች የእጃቸውን በትር ነጠቁአቸው ወደ ጌታ ቢያመለክቱ በትራቸው እባብ ሆና ነድፋ ገድላቸዋለች። መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ሀገረ ምሑር አድርሷቸውዋል። በዛም የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በመጥራታቸውና ንጉሱን አብላኝ ቢሉት የኔ አምላክ ማኮስ ነው ኢየሱስ የምትለው ማን ነው አላቸዉ? አምላካችን ነው አሉት። ወስዶ ቤተ ጣዖት ቢያሳያቸው በእግራቸዉ ረግጠው አሰጠሙት። መስፍኑ ተቆጥቶ አሰራቸው። መልአኩም ከእስራታቸው ፈቷቸዋል። እንዲያበላቸው ዳግም ሀገረ ገዢውን ቢጠይቁት ተናዶ በጦር ሊወጋቸው ሲል ምድር አፏን ከፍታ ባሕር ሆና አሰጠመችው። እንዲህ እያሉ ብዙ ስለ ጌታ መስክረዋል። ኋላም ወደ ምድረ ጉራጌ ወርደው ብዙውን አስተምረው ወደ እምነት መልሰዋል። በጸሎታቸውም ብዙ በሽተኞችን ፈውሠዋል። ሁዋላም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምንኩስና ተሰጥቷቸው ወደ ደብረ አስቦ (በደ/ሊባኖስ ተክልዬ ለ29 ዓመታት የጸለዩበት ቦታ) ሄዱ። ከዚህ በኋላ አቡነ ዜና ማርቆስ ደብረ ብስራትን ገድመው እያስተማሩ ኖረው ፪፻ አናብስት በ፪፻ አናምርት ታጅበው በደመና ተጭነው ብዙ ቦታ በመሄድ አስተምረዋል። ከእረፍታቸው በፊትም ልጆቻቸውን በሙሉ ከየሀገሩ ጠርተው ቅዳሴ ቀድሰው ሲያቆርቡ ከብዛታቸው የተነሳ ፀሐይ ልትገባ ስለሆነ ወደ ጌታ አመልክተው አቀብለው እስኪፈጽሙ ድረስ ፀሐይ ባለችበት እንድትቆም አድርገዋል። ከዚህ የበዙ ተዓምራትን ሲያደርጉ ኖረው በተስፋቸው ያመነ በኪዳናቸው የተማጸነ ዋጋውን እንደማያጣ ጌታ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው በተወለዱ በ፻፬ (140) ዘመናቸው ታህሳስ ፫/ 3/ ቀን ዐርፈዋል:: አቡነ ዜና ማርቆስ በምሁር ሀገር ይመለክ የነበረውን ማኮስ የተባለውን ጣዖት መሬት አፏን ከፍታ እንድትውጠው ካደረጉት በኃላ ሀገረ ገዥው ተቆጥቶ በአባታችን ላይ ክፉ ሲያደርግ አባታችንም ‹‹ካላመንክ አንተም እንደ አምላክህ እንደ ማኮስ መሬት ተከፍታ ትውጥሃለች›› ብለው በተናገሩበት ቅጽበት ከነሠራዊቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው፡፡ ያንን ሀገረ ገዥም ስለተጠመቁት ልጆቹና ሚስቱ ብለው ከ5 ዓመት በኋላ በጸሎታቸው ኃይል ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ያንጊዜም ጳጳሱ ጌርሎስና የሀገሩ ሕዝብ ሁሉ ይህን ተአምር አይተው እጅግ ሲደነቁ ከቆዩ በኋላ ከሞት የተነሣውን ያንን ሀገረ ገዥ ‹‹በባሕር ላይ ወድቀህ በውስጡ ከተደፈንክ በኋላ ከሞት እንዴት ተነሣህ?›› በማለት ጠየቁት፡፡ እርሱም በሲኦል ያየውን ሁሉ ከነገራቸው በኋላ በጻድቁ ዜና ማርቆስ ጸሎት እንደተነሣ ነገራቸው፡፡ ሞቶ የተነሣው ሀገረ ገዥም በሲኦል ያየውን ከተናገራቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ አንዱ ይህ ነው፡- ‹‹ሰው በክፉ ሥራው ተፈርዶበት በሲኦል ወዳለው የእሳት ባሕር ሲወርድ በሁለቱ የሰንበት ቀኖችና የፍጥረት እመቤት በሆነች በፈጣሪ ክርስቶስ እናት በቅድስት ድንግል ማርያም በዓል ቀን ወደ ውጭ አውጥተው ያሳርፉታል፡፡›› የኢትዮጵያው ጳጳስ አባ ጌርሎስ በድንገት ዐርፈው ነበር ነገር ግን አቡነ ዜና ማርቆስ ጸሎት አድርገው ከሞት አስነሥተዋቸዋል፡፡ አባታችን ዜና ማርቆስ የሚያደርጓቸው እጅግ ድንቅ የሆኑ ተአምራት በሕዝብ ዘንድ ውዳሴን እያመጣ እንዳያስቸግራቸው ብለው ይህን ተአምር የማድረግ ሥራ እግዚአብሔር እንዲያርቅላቸው ለመኑት፡፡ ከዚህም በኃላ አባታችን ወግዳ በምትባል ሀገር ሄደው በዋሻ ውስጥሳሉ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደ እርሳቸው መጥተው አብረው በዋሻው ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ቆይተዋል፡፡ ለአባ ዜና ማርቆስና ለሌሎች ለብዙ አባቶች የምንኩስና አባት የሆኑት አቡነ ተክለሃይማኖት ትሕትናቸውን ያሳዩ ዘንድ አቡነ ዜና ማርቆስን ያገለግሏቸው ነበር፡፡ ወደ ሞረት ሀገር እንዲሄዱ መልአክ ነግሯቸው ሁለቱም ሄደው በዚያም አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጣዖት አምላኪውን የሞረቱ ገዥ ሊገድላቸው ፊልጎ ከነሠራዊቱ ወዳሉበት ዋሻ ሄደ፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስም ተራራዋን በሥላሴ ስም ባርከው ቢያዟት የገዥውን ጭፍሮች አፏን ከፍታ ዋጠቻቸው፡፡ ገዥውን ድል አሰግድንም በተአምራቸው አሳምነው አስተምረው አጠመቁት፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለአቡነ ተክለሃይማኖት ተገልጦላቸው ወደ ግራርያ (ዛሬ ስሙ ተለዉጦ ሰላሌ የሚባለዉ ሀገር) እንዲሄዱ ስለነገራቸው አቡነ ተክለሃይማኖት የመላእክትን አስኬማ ለአቡነ ዜና ማርቆስ አልብሰዉ በደብረ ብስራት እንዲጸኑ ነግረዋቸው ወደ ግራርያ (ሰላሌ) ሄዱ፡፡ሲሄዱም የደብረ ብስራት ዛፎቹ እንጨቶቹና ደንጊያዮቹ ሁሉ አቡነ ተክለሃይማኖትን እንደ ንጉሥ ሠራዊት ከፊት ከኋላ ሆነው ሸኝተዋቸዋል፡፡ አባታችንም ‹‹የወንድሜን የዜና ማርቆስን ቦታ ትታችሁ ከዚህች ምድር ትሄዱ ዘንድ አልፈቅድምና ሁላችሁ በየቦታችሁ ቁሙ›› ብለዋቸዋል፡፡ ‹‹ሰውም እንኳ ቢሆን ለምንኩስና ወደ እኔ ዘንድ ወደ ግራርያ ከመምጣቱ በፊት ይህን ምድር ሳይሳለም ወደ እኔ አይምጣ›› በማለት ቃልኪዳናቸውን ከደብረ ብስራት ጋር አድርገዋል፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስ 8 እንጀራን አበርክተው 8ሺህ ሰዎችን መመገባቸውና ፀሐይን ማቆማቸው፡- ‹‹አባታችን ዜና ማርቆስ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል ጸለየ፡- ‹የምስጋናና የክብር ባለቤት ሆይ! ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በ5 እንጀራና በ2 ዓሣዎች 5 ሺህ ሰዎችን ያጠገብካቸው አንተ ነህ፣ እንዲሁ እነዚህ የተራቡ ባሮችህ ልጆቼ በልተው ይጠግቡ ዘንድ በእኔ በባሪያህ እጅ በእኒህ እንጀራዎች ላይ የቸርነትህን ጸጋና በረከትህን አድርግ› ብሎ ከጸለየ በኋላ እነዚያን ያመጡለትን 8 እንጀራዎች ባርኮ ቆራርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፣ ደቀ መዛሙርቱም እንግዶች ለሆኑ ልጆች ሁሉ አቀረቡ፣ 8ሺ መነኮሳት ልጆቹም በልተው ጠገቡ፡፡ በታኅሣሥ ወር መባቻ አባታችን የቅዳሴውን ሥርዓት ጀመረ፣ ማዕጠንት ይዞ እየዞረ የቤተክርስቲያኑን በሮች በሚያጥንበት ጊዜ ሥጋ ወደሙን ለመቀበል እርስ በእርሳቸው ሲጨናነቁ የልጆቹ መነኮሳትን ብዛት ተመለከተ፡፡ ያን ጊዜም በልቡ አሰበ፣ እንዲህም አለ፡- ‹ይህን ያህል ያለውን ሰው ቅዱስ ቊርባን ማቀበል እንዴት ይቻላል? ይህ ሁሉ ሰው በተራ እስከሚቀበል ድረስ ፀሐይ ይገባል፣ መሽቶ ሌሊትም ይሆናል› አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ዐይነ ልቡናውን ወደ ሰማይ አቅንቶ ‹አቤቱ ጠላቶቹን እስከደመሰሰና ለእስራኤል ልጆች ርስታቸውን እስካካፈለ ድረስ ለኢያሱ ፀሐይን በገባዖን ያቆምክ አንተህ፤ ዛሬም ቅዱስ ሥጋህን ክቡር ደምህን ለእነዚህ ባሮችህ ቅዱሳን መነኮሳትና ለሕዝቦችህ እስከማቀብላቸው ድረስ እንዲሁ በቸርነትህ ብዛት ፀሐይን አቁማት› ብሎ በጸለየ ጊዜ ፀሐይዋ ወዲያውኑ ቆመች፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዳሴውን ጨርሶ ሕዝቡን ሁሉ አቆረባቸው፡፡›› አባታችን ዜና ማርቆስ ወደ ዋልድባ በመሄድ ከአባ ሳሙኤል ጋር ተገናኝተው እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አባቶች በየቦታው እየሄዱ በረከት ተቀብለዋል፡፡ የተሰዓቱ ቅዱሳንን ገዳማት ተሳልመው ወደ ሰሜንም ሄደው ዜማውን ሲያዜም ያሳያቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ ያሬድ መቅደስ ሄደው ሰባት ቀን ሲማጸኑ ከቆዩ በኋላ ወደ አክሱም ጽዮን ሄደው በዚያ ከቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱስ ኤፍሬምና ከቅዱስ አባ ሕርያቆስ ጋር ሆኖ እነርሱ ድርሰታቸውን ሲያነቡ ያሬድ ደግሞ ድርሰታቸውን እያዜመው ተገልጠውላቸዋል፡፡ ወደላሊበላም ሄደው ከቅዱስ ላሊበላ በረከትን ተቀብለዋል፡፡ ወደ ጣና ደሴትም ሄደው በዚያ ካሉ ቅዱሳን ተባርከዋል፡፡ ሐይቅ እስጢፋኖስም አባ ኢየሱስ ሞዐ ጋር በመሄድ እንዲሁ ተባርከዋል፡፡ በታናሽ ደመናም ወደ ብሔረ ሕያዋን ተነጥቀው ሞትን ካልቀመሱት ከሄኖክ፣ ከኤልያስና ከዕዝራ በረከትን ተቀብለዋል፡፡ ወደ እስላም ሀገርም በመሄድ ለአንድ ዓመት ቆይተው በዚያ ያሉ ሕዝቦችን በተአምራቸውና በትምህርታቸው አሳምነው አጥምቀዋቸዋል፡፡