У нас вы можете посмотреть бесплатно DW Amharic የመጋቢት 06 ቀን 2018 የዓለም ዜና или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
• የኢትዮጵያ መንግሥት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋ ላይ ያደረገውን ጭማሪ ተከትሎ በአዲስ አበባ የሕዝብ መጓጓዣ ታሪፍ ከ5 እስከ 20 ብር የሚደርስ የታሪፍ ማሻሻያ ተደረገ። • የሩሲያ ጦር በዩክሬን በመካሔድ ላይ ለሚገኘው ጦርነት ኬንያውያንን በግዳጅ ከመመልመል እንዲታቀብ ግፊት ለማድረግ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ ዛሬ እሁድ ወደ ሞስኮ አቀኑ። • በመካከለኛው አፍሪካዊቷ ሀገር ኮንጎ-ብራዛቪል ዛሬ እየተካሔደ በሚገኘው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ዜጎች ድምጽ ሲሰጡ ዋሉ። • አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን የገጠሙትን ጦርነት የቀሰቀሱ መሪዎች ውጊያውን እንዲያስቆሙ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ ጥሪ አቀረቡ። ጦርነቱ 16ኛ ቀኑን ዛሬ ሲያገባድድ እስራኤል እና ኢራን የሚፈጽሟቸውን ጥቃቶች ቀጥለዋል። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ሥምምነት ላይ ለመድረስ ፍላጎት አላት ቢሉም የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ለተኩስ አቁምም ይሁን ለድርድር ጥያቄ እንዳላቀረበች ተናግረዋል። • ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በስፔን ባርሴሎና እና በደቡብ ኮሪያ ሴዑል የተካሔዱ የማራቶን የሩጫ ውድድሮችን አሸነፉ።