У нас вы можете посмотреть бесплатно የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ የሥራ አፈጻጸም 2024/25 First Half Year Business Performance Full Video или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ኩባንያችን በበጀት አመቱ አጋማሽ 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ብዛት 80.5 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን ከእቅድ አንጻር አፈጻጸሙ100% ሆኗል፡፡ ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ5.9 ሚሊዮን ወይም የ7.9% እድገት አሳይቷል፡፡ በዚህም ከአፍሪካ 1ኛ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ 17ኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን በቅርቡ በጂ.ኤስ.ኤም.ኤ (GSMA) ጥናት ተረጋግጧል። የቴሌብር አገልግሎት በ2017 የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት 5 ሚሊዮን ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የአገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር 51.5 ሚሊዮን በላይ በማድረስ የዕቅዱን 99.8% አሳክቷል፡፡ በግማሽ ዓመቱ በቴሌብር 1.03 ትሪሊዮን ብር የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር የተከናወነ ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 3.58 ትሪሊየን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ በኢኮኖሚው ውስጥ ማንቀሳቀስ ተችሏል፡፡ ይህም የገንዘብ ዝውውርን ቀላል እና ቀልጣፋ በማድረግ አካታችና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት በማስቻል ላይ ነው፡፡ በጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ኩባንያችን በማህበራዊ ኃላፊነት ረገድ በድምሩ ከ287.17 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለሰብአዊ ድጋፍ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአረንጓዴ ልማትና ማስዋብ እንዲሁም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች የተደረገ ሲሆን፣ በዓይነት 131.3 ሚሊዮን ብር፣ በገንዘብ ደግሞ ከ155.9 ሚሊዮን ብር በላይ ነው። ለተጨማሪ https://bit.ly/40RlnYV ይጫኑ #CSR #Ethiotelecom #telebirr #GSMA #ITU #WorldBank #OECD #G6countries #HOPR #HoF