У нас вы можете посмотреть бесплатно DW Amharic የመጋቢት 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
የመጋቢት 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና • አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን በገጠሙት ጦርነት ምክንያት ለኢትዮጵያ ነዳጅ የሚያቀርቡ ሀገራት በውላቸው መሠረት ማቅረብ እንደማይችሉ ማሳወቃቸውን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ተናገሩ። ሚኒስትሩ ዶክተር ካሳሁን እንዳሉት ለኢትዮጵያ ገበያ በየቀኑ ይቀርብ የነበረው ነጭ ናፍጣ ከ9.2 ሚሊዮን ሊትር ወደ 4.5 ሚሊዮን ሊትር 50 በመቶ ገደማ ቀንሷል። • የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በበኩሉ በመካከለኛው ምሥራቅ በመካሔድ ላይ በሚገኘው ጦርነት ምክንያት የተፈጠረው ቀውስ በኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ላይ “አሉታዊ ተጽዕኖ” እንደሚኖረው ገልጿል። • የሶማሊያ ጦር የደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ ግዛት ትልቅ ከተማ የሆነችው ባይዶዋን ተቆጣጠረ። የግዛቲቱ ፕሬዝደንት አብዲአዚዝ ሐሰን ሞሐመድ ከሥልጣን ለቀዋል። • እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነትና የኢራን አፀፋ የመካከለኛዉ ምሥራቅ ሐገራትን ማዉደሙን ዛሬም ለሁለተኛ ወር እንደቀጠለ ነዉ። ጦርነቱ እንዲቆም ፓኪስታን እና ቻይና ዛሬ ጠይቀዋል • እስራኤል በጦር ፍርድ ቤቶች ጥፋተኛ የተባሉ ፍልስጤማውያን ሁሉ በስቅላት እንዲቀጡ ያጸደቀችው ሕግ እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ የአውሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ሥጋቱን ገለጸ። የእስራኤል ምክር ቤት (ክነሴት) ያጸደቀው ሕግ ከፍተኛ ተቃውሞ እና ትችት እየቀረበበት ነው።