У нас вы можете посмотреть бесплатно 🛑ከ "62_ ዓመት በፊት ስለ ነብዩ ሙሀመድ የፃፉት ደራሲ ተሸለሙ! или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
@YeMelkamsewFamily1 #like_share_subscribe_comments የደራሲ ወልደገብርኤል አሰጌ የሕይወት ታሪክ ደራሲ ወ/ገብርኤል አሰጌ በደብረታቦር ከተማ በ1926 ዓ.ም ተወለዱ። አራት ዓመት ሲሞላቸውም ፊደል ቆጠሩ። በወቅቱ በነበረው የጣልያን ወረራ ምክንያትም የእናታቸው ሀገር ዘጌ (ጎጃም) ያቀኑ ሲሆን እስከ 15 ዓመታቸውም በዚያው በዘጌ ቆይተዋል። በ12 ዓመታቸው ዳዊት ደግመዋል። ደራሲ ወ/ገብርኤል ወደ ደብረታቦር ተመልሰው ዘመናዊ ትምህርት የተከታተሉ ሲሆን እስከ 7ኛ ክፍል ከተማሩ በኃላ በ1943 ዓ.ም ወደ ጎንደር አቅንተው በጎንደር ሆስፒታል በተላላኪነት ተቀጠሩ።በ1946 ዓ.ም ወደ ደብረታቦር በመመለስ ያቋረጡት ትምህርት ቀጠሉ። ወደ ጎንደር አቅንተውም ጎንደር ሆስፒታል አገልግለዋል። በወቅቱ በደብረሲና በተከሰተው የታይፈስ ህመም ወረርሽኝ ለማከም ሆስፒታሉ መድቧቸው ሠርተዋል።በወቅቱ ታይፈስ ያለበት ቤት የገባ ጤነኛ ሰው በበሽታው ይያዛል የሚል የተዛባ አመለካከት በመኖሩ ህመምተኞች ለብቻቸው ተገለው ይቀመጡ ነበር። ደራሲ ወ/ገብርኤልም ለታማሚዎች አስፈላጊ ህክምና ከመስጠት ባለፈ የታካሚዎችን የግል ንፅህና በመጠበቅም እርዳታ አድርገው ነበር። ደራሲ ወልደገብርኤል ፣በጎንደር ሆስፒታል እያገለገሉ የተለያዩ ፅሁፎች የፃፉ ሲሆን በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ፤በአዲስ ዘመን እንዲሁም በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ የገበሬውን ህይወት የሚያስቀኝ፤ስለመንግስት አስተዳደር የተለያዩ ፅሁፎችን ፅፈው አስነብበዋል።በተለይ በ1954 "ባህል እና ኢኮኖሚ" የሚል ጋዜጣ ላይ በገበሬዎች ላይ ስለሚፈፀመው የከብት ዝርፊያ ከችግሩ መንስኤ እስከ መፍትሔ ያቀረቡት ፅሁፍ ከፍተኛ አድናቆት አትርፎላቸው ነበር። እርሳቸው ከጋዜጣ መጣጥፎች ባሻገር የተለያዩ ቲያትሮች የደረሱ ሲሆን 'የህይወት ዘበኛ ' የተሰኘ ቲያትራቸው ትኩረቱን አንድ አስታማሚ ታማሚን በምን መልኩ መርዳት እንዳለበት የሚገልፅ ነበር። በኃላም ቲያትሩ በመፅሀፍ መልክ ታትሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ወህኒ ቤቶች 6,000 ኮፒ አከፋፍለዋል። ደራሲ ወ/ገብርኤል የጎንደር ማተሚያ ቤት ሲቋቋም አንስቶ የነበሩ ሰው ናቸው። በጎንደር ከተማ ልማት እና ቅርስ ላይ ትኩረቱ ያደረገው "ትዕይንተ ጎንደር" ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት በፀሀፊነትም ረዘም ላለ ጊዜም አገልግለዋል። ደራሲ ወ/ገብርኤል ልዑል አለማየሁ፤ ጄነራሉ ሙሽራ እንዲሁም የነብዩ የመሀመድን ታሪክ የሚያወሳ መፅሀፍ ፅፈዋል። ደራሲ ወ/ገብርኤል በጎንደር ከተማ በነበሩበት ጊዜ በማተሚያ ቤት፤በርስት ክፍል፤በህዝብ እና ቆጠራ የሥራ መደቦች አገልግለዋል። ደራሲ ወልደገብርኤል በአሁኑ ሰዓት ነዋሪነታቸው ካሊፎርኒያ ሳንሆዜ ከተማ ሲሆን በዚሁ በሳንሆዜ ከተማ በተለያዩ የማህበረሰብ አገልግሎት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ይታወቃሉ። ደራሲ ወልደገብርኤል ከ62 ዓመት አስቀድሞ የነቢዩ መሐመድ ታሪክ በሚል ርዕስ መፅሀፍ ለህትመት በማብቃታቸው በሥነፅሁፍ እና በታሪክ ዘርፍ የዘንድሮው 7ኛውን ዙር 2026 ዓ/ም የጷግሜን አዋርድ ሽልማት እንዲሸለሙ ከውሳኔ ላይ ተደርሷል። በመሆኑም ለደራሲ ወ/ገብርኤል ቤተስብ እና አድናቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ጳጉሜን የኢትዮጵያውያን መዝናኛ እና ባህል ማዕከል በሎስ አንጀለስ ካሊፎርኒያ መልካም ምኞቱን ይገልጻል::