У нас вы можете посмотреть бесплатно ጸሎተ ፍትሐት፣ በዶርማገን ( Dormagen ) በግፍ ለተገደለው ታዳጊ ልጃችን ዮሴፍ ( ገ/እግዚአብሔር ) የተደረገ ጸሎተ ፍትሐት። или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
✥ የጉዞ ፍትሐት ✥ ጥያቄ ፡- የጉዞ ፍትሐት 7ቱ ትርጉምና ምሳሌው ምንድን ነው ? ሰው ሲሞት ወደ መቃብሩ በሚጓዝበት ጊዜ በ 7 ምዕራፍ 7 ጊዜ ጸሎተ ፍትሐት ማድረስ ይገባል ይኸውም እስራኤል የኢያሪኮ ከተማ 7 ጊዜ እየዞሩ በጸለዩ ጊዜ ቅጽሩ ፈራርሶ ወድቋል ፡፡ ኢያ ፯፥፭ የዘመነ ሐዲስ ካሕናትም ጽናውን ( ማዕጠንቱን ) ይዘው እያጠኑ “በከመ እንሀልከ ቅድመ ጥቅማ ለኢያሪኮ በእደ ኢያሱ ገበርከ ከማሁ እንህል ኃጢአትየ ወኃጢአተ ኩሉ ሕዝብከ በእደ ዚአየ ( ጸለተ እጣን ) እያሉ ቤተክርስቲያኑን 7 ጊዜ እየዞሩ የምእመኑን ኃጢአት ደምስስ በማለት ይጸልያሉ በሞተውም ምእመን በዚሁ ምሳሌ 7 ጊዜ እየጸለዩ ቅጽረ ኃጢአት አፍርስለት ( ማረው ይቅር በለው እያሉ ጸለተ ፍትሐቱን ያደርሱለታል፡፡ ዳግመኛም ነቢይ ኤልሳዕ የሞተውን ሰው 7 ጊዜ ጸልዮ አስነስቶታል ‘‘ወሰከበ ኤልሳዕ ላዕለ ውእቱ ሕፃን ወጸለየ እስከ ሳብዕ ነገ ካልዕ ፬፥፴፫ ብሏልና የዚህ ምሳሌ ነው ነገርግን “ወይፈድዩ ለኵሉ በከመ ምግባሩ” ባለው መሰረት ሰው የሚጸድቅና የሚኮነን እንደ ስራው እንጂ ካህናት ፈትተውት አያጸድቁ አስረው አያጠብቁ አንዳይባል በምድር ያሰራችሁት በሰማይ የታሰረ በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይሁን ብሎ በምድርም በሰማይም የሚያስር የሚፈታ ስልጣን እንደሰጣቸው በማስታወስ አለ ማቴ ፲፰፥፲፰ ምሳሌውን ባወቀ አስመስሎታል ምስጢሩንስ ? ቢሉ ሳብዕ (ሰባት) ሲባል ሰባት ነገር ያለው ሰው ማለት ስለሆነ በሰባት ነገር ተደፋፍሮ የፈጸመውን ኃጢአቱን ይቅር ብለህ ማርልኝ ብሎ መጸለይ ሰባት ነገር የተባሉትም አራቱ ባሕርያተ ሥጋና (ውኃ፣ነፋስ ፣መሬት ፣ እሳት) ሦስቱ ግብራተ ነፍስ (ነባቢት ፣ ለባዊት ፣ ሕያዊት) ናቸው፡፡ እንዲሁም በዕብራውያን አቆጣጠር ሰባት ቁጥር ፍጹም ስለሆነ የሞተውን ምእመን መንግስተ ሰማያት ለማግባት ፍጹም አድርግልን ብሎ ለመለመን ነው፡፡ ‹‹እስመ ኁልቁ ሳብዕ በኀበ ዕብራውያን ፍጹም ውእቱ›› እንዳለ የ7 ፍጹምነት በሰባቱ ፊደላት በሰባቱ ዕለታት አቆጣጠር የሚታወቅ ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት‹‹ሰብዐ ለዕለትየ እሴብሐከ›› በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንኃለው ያለውን ያስታውሳል። (መዝ 118፥164) ይቆየን ✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተሰፋዬ