У нас вы можете посмотреть бесплатно መልክአ ገብረ መንፈስ ቅዱስ //ወር በገባ በ5 በየወሩ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና የሌሎችም ቅዱሳን ወርዓዊና አመታዊ ክብረ በዓላቸው በድምቀት ይከበራል// или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
#famfan3 #ethiopianorthodox #ethiopia #duet #habesha #አቡነ_ገብረመንፈስ_ቅዱስ ስለሕዝብ ሁሉ ሲፀልይ እንባው በጉንጮቹ ላይ እንደ ውኃ የሚፈስ፣ የማይሰለች ተጋዳይ፣ የክብር ኮከብ፣ የገዳም መብራት፣ ስም አጠራሩ የተመሰገነ ደግ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ። ውዳሴ ከንቱነትን አለምንና በአለም ውስጥ ያለውን ሁሉ ጠላ ከሰው ተለይቶ ወደ ጫካ ገባ በዚያም ኖረ፤ በበጋው ሐሩር በክረምት ቁር እየተሰቃየ ኖረ፡፡ በሰውነቱ ላይ ልብስን አለበሰም እራቁቱን ነበር እንጂ፡፡ ራቁቱን በብርድ ላይ ቆሞ ይጸልይ ነበር፤ ወገቡንም በማቅ በሠንሠለት ታጥቆ ነበር ከዚያ ጫካ ቅዝቃዜ የተነሳም ሰውነቱ አልቆ አጥንቱ ደርቆ ነበር፡፡ ሰውነቱንም በእግዚአብሔር ፊት ዕራቁትሽን ትቆሚያለሽና እወቂ ጽኚ በርቺ ጨክኝ ይላት ነበር፡፡ እንደዚህ ባለ ስራ በጾምና በጸሎት በስግደትና በብዙ ትጋት ቀንም ሌሊትም ጽሙድ ሆኖ ያለ ዕረፍት ብዙ ጸሎትን ይጸልይ ብዙ ስግደትን ይሰግድ ነበር፡፡ ሥጋው እስኪደርቅ ቁርበቱም ከአጥንቱ እስኪጣበቅ ድረስ ከእንጨት ፍሬና ሥራ ሥር ወይም ከአትክልት ወይም ገዳማውያን ከሚመገቡት ከሌሎች ፍሬያት ምንም ምን የሚመገበው አልነበረውም ለሥጋውም ምንም ምን ምክንያት አልሰጠም፡፡ ስሙ ገብርኤል የሚባል መልአክም ደብረ ቅዱስ ወደሚባለው ወደ ዝቋላ ወሰደው አባታችንም በውኃ ዳር ቆሞ በ4ቱም አቅጣጫ ተመለከተ የኢትዮዽያን ሰዎች ኃጢአትም አየ፥ በፊቱም የተገለጠ ሆነ። ይህን ባየ ጊዜ ወደ ባሕር ተወረወረ ቁልቁልም ተዘቅዝቆ ‹ከባሕር እንዳልወጣ በእግሬም እንዳልቆም በሕያው ስምህ እምላለሁ› እያለ እንዲህ ሆኖ 40 መዓልትና 40 ሌሊት ቆየ። ‹ስምህን የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሃለሁ› የሚል ቃል ወደ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ መጣ፤ ገብረ መንፈስቅዱስም መልአኩን እንዲህ አለው ‹ መላ ኢትዮዽያን ካልማረ ከዚህ ባሕር አልወጣም › ያም መልአክ ከእሱ ዘንድ ሄደ፤ ዘወትር በጸሎቱ የማይረሳት ኢትዮጵያን ‹‹ አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ ›› ይላል። እንዲህ ባለ ተጋድሎ በዚያ ባሕር ውስጥ 100 ዓመት ኖረ። ሥጋው አለቀ ደሙም በባህር ውጥ ፈሰሰ ውኀውም ደም መሰለ አጥንቶቹ እንደ በረድ ሆነው ታዩ። ሰባት ሺህ እልፍ ሦስት መቶ አጋንንት በየቀኑ ይመጡ ነበር በፍላጾቻቸውም ይወጉት ነበር፤ እስከ መቶ ዓመት ድረስ አጥንቱን በሻፎ (ሱፋጭ) ደንጊያ ይፈጩት ነበር ገድሉ መከራው ትዕግስቱ ብዙ ነበር። ከዚህ በህዋላ ጌታችን ወደርሱ መጥቶ ከባሕር ዳር ቆመ አባታችንንም ተነስ ውጣ መላው ኢትዮዽያን ምሬልሃለሁ አለው። አጥንቱ እንደ መርፌ ቀዳዳ ተበሳስቶ ተገኘ ጌታም ሁለንተናውን ዳሰሰው እንደቀድሞ ደኅና አደረገውና ወደ ምድረከብድም ላከው። ወደላይ ወጥቶ ከፀሐይ በላይ ከሰማይ በታች እስከ ሰባት ዓመት ኖረ። ከዚህም ቡሀላ ወደ ምድረ ከብድ ተልኮ እንደ አምድ ትኩል ሆኖ ሰባት ዓመት ቆሞ ቆየ ፣...... አቡነ ገብረ-መፈስ ቅዱስ