У нас вы можете посмотреть бесплатно ተአምሯን ዕንስማ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ምሥጢረ ጥምቀት፦ ሀ. የማጥመቅ ሥልጣን የተሰጠው ለነማን ነው? ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ሒዱና አሕዛብን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቁ” ብሉ የላካቸው ሐዋርያቱን ነው፡፡ ሐዋርያት ደግሞ እናንተ ያሰራችሁት የታሰረ የፈታችሁት የተፈታ ይሆናል” በማለት የክህ ነት ሥልጣን ከጌታ የተሰጣቸው ካህናት ናቸው፡፡ (ማቴ.18+18) ስለዚህ የማጥመቅ ሥልጣን የተሰጠው : ለቀሳውስት ብቻ ሲሆን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሰረት ምእመን የማጥመቅ ሥልጣን የለውም፥ ሥልጣነ ክህነት በሌላው ሰው የሚደረግ ጥምቀት የውኃ እጥበት እንጂ ጥምቀት አይባልም። ሊ የሥነ ምግባር ጉድለት ያለበት ቄስ የሚያጠምቀው ጥምቀት እንደ እውነተኛ ጥምቀት ተቆጥሮ ልጅነትን ያሰጣልን? ጥምቀት የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ በመሆኑ በአጥማቂው ስው ስብእና ላይ አይመሠረትም፡፡ ካህኑ የሰጭው የእግዚአብሔር መገልገያ መሣሪያ ነው። በጥምቀት የሚገኘው ጸጋ በእውነተ ኛውና ንጹሐ ባሕርይ በሆነው በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ላይ የተመሰረተ እንጂ አጥማቂው በሥነ ምግባሩ እንከን ያለበት ቢሆን ተጠማቂው በሚያገኘው ጸጋ ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም፡ ዳሩ ግን በራሱ በአጥማቂው ላይ የእግዚአብሔር ፍርድ ይጠብ ቀዋል፡፡ የሚከተሉት ምሳሌዎች ከላይ የተገለፀውን እውነታ ግልጽ ያደርጉልናል። አጥማቂው ካህን የምሥራች ቃል የሰፈረበትን መልእክት ይዞ የመጣ ሰውን ይመስላል፣ መልእክቱን ይዞ የመጣው ሰው መልከመልካም ይሁን መልከ ጥፉ ፣ ጸባየ መልካም ይሁን መጥፎ ይዞት በሚመጣው መልእክት ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡ እንዲሁም አጥማቂው ካህን በመሬት ላይ ዘርን የሚዘራ ገበሬን ይመስላል፡፡ አንድ ገበሬ ጠባዩ ጥሩ ይሁን መጥፎ በሚዘራው እሀል ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡ ጥሩ ዘርን በጥሩ መሬት ላይ ከዘራ ጥሩ ምርት ይገኛል፡፡ ዳሩ ግን አዘራሩን ማሳመር ነው፡፡ የአዘራሩን ሥርዓት ተከትሎ ጥሩውን ዘር ከዘራ ኃጥእ ገበሬ ዘራው ጻድቅ ገበሬ በሚዘሩት ምርት ላይ ለውጥ አያመጣም። ሐ. ድኅነት በጥምቀት ነው ከተባለ ከጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ መቼ ተጠምቆ ነው የዳነው? የጥምቀት ባሕርይውና ዓላማው አንድ ሲሆን የተለያዩ አካላት እንዳሉት የጥምቀት ዓይነት በሚለው ርእስ ማየት ይቻላል፡፡ በዚህም መሠረት ለውኃ ጥምቀት ሳይደርሱ በመንገድ ላይ ሳሉ በክርስቶስ በማመናቸው በዕሳት በስለት አማካኝነት የሞት ጽዋን የተጎነጩ ሰማዕታት የተጣሉበት ዕሳት ባሕረ ጥምቀት የፈሰሰው ደማቸው ደመ ጥምቀት ይሆንላቸዋል።(ሮሜ 6፥5) ማቴ 10፥32 ማቴ.16፥25: በጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ በክርስቶስ አምኖ በመንግሥትህ አስበኝ ባለው ጊዜ በመስቀል ላይ የፈሰሰው የክርስቶስ ደም ለእርሱም ሆነ ከጌታ ሞት በፊት በሲኦል ለነበሩት ነፍሳት ሁሉ ጥምቀት ሆኖላቸው የልጅነት ጸጋ ተጐናጽፈው ከሲኦል ወደ ገነት ተዘዋውረዋል፡፡ መ. ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የወኅኒ ጠባቂው “እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል?” ብሎ _ በጠየቀው ጊዜ “በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተሰቦችህም ትድናላችሁ" ለምን አለው? ለምን ተጠመቅ አላለውም።የሐዋ.ሥራ 18+30። "ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም። ዕብ.11፥6 ስለዚህ እምነት ለድኅነት መሠረት ነው፡፡ ሳያምኑ ለዚህም ነው ለጽድቅ የሚያበቃ ሥራ ለመሥራት አይቻልም። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለመዳን ምን ላድርግ ላለው ሰው በቅድሚያ እምነት ሊኖረው እንደሚገባ ያስገነዘበው፡፡ ያለእምነት የሚደረግ ጥምቀት የሰውነትን እድፍ ለማስለቀቅ የሚደረግ እጥበት እንጂ ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና የሚያስገኝ እይሆንም፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ሕፃናት የሚጠመቁት የወላጆቻቸውን እምነት መሰረት በማድረግ ነው፡፡ የክርስቲያን ልጅ ክርስቲያን ሊሆን ይገባዋልና ካደጉ በኋላ ወደ ቤተክርስቲያን በንስሐ የሚቀርቡ ወገኖች ሁሉ አስቀድመው ማመን ይኖርባቸዋል፡፡ አእምሮአቸው _ በእምነት ከታነጸ በኋላ ወደ ጥምቀትና ሌሎች ምስጢራት ያመራሉ፡፡ የወኅኒ ጠባቂውን ሀኔታም በአግባቡ ካጤነው ከእምነት በኋላ ጥምቀትን መፈጸሙን እንረዳለን፡፡ “ያን ጊዜውንም እርሱ ከቤተሰቦቹ ሁሉ ጋር ተጠመቀ( የሐዋ.ሥራ 16፥33፡፡) ሠ. በአንዳንድ ሰዎች አመለካከት ጥምቀት በውኃ የሚደረግ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ የሚደረግ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማትና ለቃሉም በመገዛት የሚገኝ ጸጋ ነው በማለት የሚከተሉትን ጥቅሶች አስረጅ አድርገው ያቀርባሉ። 1ኛ.ጴጥ.1፥23፣ ያዕ.1-18። ጥምቀት የሚለው ቃል ትርጉም ከመነሻው እንደተገለጸው ውኃ ውስጥ መነከርና መውጣትን የሚያመለክት ነው። ጌታም “ሰው ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር..." በማለት የገለጸውም በውኃ በመነከርና ቅብዓ ሜሮን በመቀባት የሚገኘው ማኅተመ መንፈስ ቅዱስን ለማመልከት ነው፡፡ ቃሉን መስማት ወደ እምነት ያደርሳል፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማ ባልሰሙትስ ረው “ያላመነበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ? ሮሜ 10+14፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ማስተማር ለሁሉም መሰረታዊና አስፈላጊ ነው። በቃሉም መሰረት __ ሕይወት መሆኑ የማያጠያይቅ ይህ ማለት ግን ቃሉን መስማት ብቻ እንደሚገኝ የታወቀ ነው፡፡ ጥምቀት ይሆናል ማለት አይደለም፡፡ “በውኃ መታጠብና በቃሉ አንጽቶ እንዲቀድሳት..." በሚለው አነጋገር የውኃ ጥምቀት የግድ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡ “ዳግመኛም የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም” ሲል በጥምቀት ዳግመኛ ከሥላሴ መወለዳችን ለኅልፈት ለጥፋት አለመሆኑን ማለፍ፡ መጥፋት ካለበት ባሕርይ እንዳልተወለድን የዘለዓለም ልጅነት ከሚያሰጥ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅዐነ ዮርዳኖስ መወለዳችንን ሲገልጥ ነው። ጌታም እንዳስገነበበን “ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነውና::" ዮሐ.3፥6፡ እንግዲህ እምነት በመስማት ነው መስማትም ከቃሉ ከ ለሁሉም መሰረት ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ በእግዚአብሔር ቃል ሁሉም ይከናወናል ጥምቀቱ ቁርባኑ ሌሎቹ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ቃል መሠረት የሚከናወኑና እንዲሁ በዘፈቀደ የሚፈጸሙ ባለመሆናቸው በቃሉ ላይ መመሥረት እንዳለብን የታወቀ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን ጥምቀት አያስፈልግም የሚል አይደለም። በብርሃነ መለኮቱ የተገለጠው መንፈስ ቅዱስ ያጽናን ይርዳን⛪️✝️ with CameraFi Live