У нас вы можете посмотреть бесплатно ከትላንቱ የእሳት አደጋ በኋላ፤ የመርካቶው “ሸማ ተራ” እንዴት ዋለ? | Ethiopia | | Addisababa | merkatofire | zena или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
በአዲስ አበባ ከተማ፤ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፤ መርካቶ ገበያ በተለምዶ “ሸማ ተራ” በተባለው አካባቢ ትላንት ሰኞ ምሽት የደረሰውን የእሳት አደጋ ተከትሎ፤ በዛሬው ዕለት በአቅራቢያው ባሉ ህንጻዎች እና መደብሮች የንግድ እንቅስቃሴ ቆሞ ውሏል። በእሳት አደጋው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት "ነባር የገበያ ማዕከል" በተሰኘ ህንጻ፤ ዛሬም ጭስ ይታይ እንደነበር በስፍራው የተገኘው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ ተመልክቷል። የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊሶች አደጋው የደረሰበትን ስፍራ ዙሪያውን በገመድ ማጠር፤ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ነጋዴዎች ወደ ቦታው እንዳይጠጉ ሲከለክሉ ተስተውለዋል። የተወሰኑ ነጋዴዎች ከቃጠሎ የተረፉ ንብረቶቻቸውን እንዲያወጡ ተፈቅዶላቸው፤ ጉዳት ወደ ደረሰበት ህንጻ ሲገቡም ዘጋቢው ታዝቧል። ትላንት ሰኞ ጥቅምት 11፣ 2017 ከምሽቱ አንድ ሰዓት ገደማ በደረሰው እና ለአራት ሰዓታት ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር ባልተቻለው በዚህ የእሳት ቃጠሎ፤ በገበያ ማዕከሉ ስር ያሉ የንግድ ቤቶች ሙሉ ለሙሉ መውደማቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ከቃጠሎው ለማምለጥ ከገበያ ማዕከሉ ህንጻ ላይ ዘልለው የወረዱ ሁለት ግለሰቦችን መመልከታቸውን ነዋሪዎቹ ለ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በዚህ ሳቢያ አንደኛው ግለሰብ “ህይወቱ ወዲያው ማለፉን”የሚገልጹት ነዋሪዎቹ፤ ከህንጻው ላይ የዘለለው ሌላኛው ግለሰብ ግን ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ደርሶበት ወደ ህክምና ተቋም መወሰዱን አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ፤ በእሳት አደጋው ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተቋማት የተወሰዱ ሰዎች መኖራቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል። ሆኖም በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር በትክክል ምን ያህል እስካሁን እንዳልታወቀ አቶ ንጋቱ ዛሬ ረፋዱን በሰጡት መረጃ ገልጸው ነበር። ስለ አደጋው መንስኤ የተጠየቁት አቶ ንጋቱ “[አደጋው] በምን ምክንያት እንዳጋጠመ እስካሁን አልታወቀም። ማጣራት እየተደረገ ነው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። እርሳቸው ይህን ቢሉም፤ የአካባቢው ነዋሪዎች ግን የእሳት አደጋው “ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ሊሆን ይችላል” የሚል ስጋታቸውን ለ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አጋርተዋል። የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦ ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider