У нас вы можете посмотреть бесплатно የየካቲት 23 ሥንክሳር или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት 23 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅድስ ስም የካቲት ሃያ ሦስት በዚች ቀን የክቡር ፋሲለደስ ልጅ የከበረ አውሳብዮስ በሰማዕትነት ሞተ ። ይህም የከበረ ፋሲለደስ ለአንጾኪያ መንግሥት የሠራዊት አለቃ ነው ለመንግሥት ልጆችም አባታቸው ነው እርሱም ከፋርስ ሰዎች ጋር በጦርነት ውስጥ እያለ ዲዮቅልጥያኖስ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክርስቶስን ክዶ ጣዖትን እንዳመለከ ሰማ ። እጅግ አዝኖ ወደ ልጁ ወደ አውሳብዮስ ልኮ ይህን ነገረው የከበሩ የቤተ መንግሥት ሰዎች ዘመዶቹን ዳግመኛ ጠራቸው እነርሱም የንጉሥ ልጅ ዮስጦስ አባዲር ገላውዴዎስና ቴዎድሮስ ከእርሳቸውም ጋርያሉትን ጠርቶ ስለ ከሀዲው ንጉሥ ነገራቸው ። ሁሉም እጅግ አዘኑ ዳግመኛም እንዲህ አላቸው እኔ ስለ ፈጣሪዬ ስለ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈሳለሁ ሁሉም በዚህ በጎ ምክርተስማምተው እርስ በርሳቸው ተማማሉ ። ጠላቶቻቸውንም ድል አድርገው ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ ንጉሡ ከሠራዊቱ ጋርወጥቶ በደስታ ተቀበሏቸው ። ከዘህም በኋላ የቅዱስ ፊቅጦር አባት ህርማኖስ ለቅዱሳኑ ጣዖትን እንዲአቀርብላቸውና አንዲሰግዱለት ንጉሡን መከረው ንጉሡም ህርማኖስ እንደ መከረው አደረገ ። በዚያንም ጊዜ ቅዱሳንን ጠርቶ እነዲህ አላቸው እኔ እጅግ እንደምወዳችሁ እናንተ ታውቃላችሁ አሁንም ለአጵሎን ሰግዳችሁ ልቤን ደስ ታሰኙ ዘንድ ከእናንተ እሻለሁ ። ቅዱሳንም ሰምተው እጅግ ተቆጡ አውሳብዮስም ንጉሡን ሊገድል ሰይፉን መዘዘ ንጉሡም ሸሽቶ ተሸሸገ ከንጉሥም ባለሟሎች ብዙዎችን ሠራዊቱንም ጭምር ገደለ የከበረ ፋሲለደስም ባይከለክላቸው ከንጉሥ ቤት ምንም ሰው ባልቀራቸው ነበር ። ከዚህም በኋላ ደግሞ አውሳብዮስን ወደ ግብጽ አገር ወስደው በዚያ ይገድሉት ዘንድ ህርማኖስ ንጉሡን መከረው እርሱ በዚች ሀገርከኖረ ያገር ሰዎችን በላይህ ያስነሣብሃልና ያሰብከውን ምንም ምን መሥራት አትችልም አለው ። ንጉሡም ቅድስ አውሳብዮስን ጽኑዕ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ ወደ ግብጽ አገር ወደ ቅፍጥ ገዥ ሉልያኖስ ዘንድ እንዲወስዱት ጻፈ ወደ መኰንን ሉልያኖስም በደረሰ ጊዜ በመንኰራኵር ሕዋሳቱን በመቁራረጥ በግርፋት አሰቃዩት ። ደግመኛም በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ አዳነው አጽናንቶና አረጋግቶ ያለ ጉዳት አስነሣው ። ነፍሱንም ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ወሰዳት የጻድቃንና የሰማዕታትንም መኖሪያ አየ ለርሱና ለአባቱ ለዘመዶቹም ያዘጋጀላቸውን ቦታዎች አይቶ ነፍሱ እጅግ ደስ አላት ። ከዚህም በኋላ ወደ እሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአከ ወርዶ እሳቱን እንደ ጠል አቀዝቅዞ ያለ ጥፋት የከበረ አውሳብዮስን አወጣው ። መኳንንቱም እንዲህ ብለው መከሩት መኰንን ሆይ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ እዘዝ ከእርሱም ትግል ታርፋለህ እርሱም የአውሳብዮስን የከበረች ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት የምሥራቃዊ ቴዎድሮስ አገልጋይ የአውስግንዮስ የምስክርነቱ መታሰቢያ ነው ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን ። አምላከ ቅዱሳን ሰማዕታት ጽናታቸውን አድሎ ከበረከታቸው ይክፈለን ። የካቲት ፳፫ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩.ቅዱስ ፖሊካርፐስ ሐዋርያዊ ሰማዕት የሰርምኔስ ዻዻስ ፪.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት አባቶቻችንን አድዋ ላይየረዳበት ፫.ቅዱስ አውሳብዮስ ሰማዕት የቅዱስ ፋሲለደስ ልጅ ፬.ቅዱስ አውስግንዮስ ሰማዕት ወርኀዊ በዓላት ፩.ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ፪.ቅዱስ ሰሎሞን ንጉሠ እስራኤል ፫.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ ፬.አባ ሳሙኤል ፭.አባ ስምዖን ፮.አባ ገብርኤል በሰርምኔስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልዐክ እንዲህ ብለህ ጻፍ:- ሞቶ የነበረው: ሕያውም የሆነው: ፊተኛውና መጨረሻው እንዲህ ይላል:- 'መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን: የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ ። ራእይ ፪፥፰ @እናታችንማርያምሆይእንወድ @yekidusantarik @Donkeybego