У нас вы можете посмотреть бесплатно ከንቲባ አዳነች አቤቤ የጉሊት እናቶችን ሰርፕራይዝ አደረጉ አዲስ አበባ Addis Ababa или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ዛሬ በልደታ ክፍለ ከተማ በፀሐይና በብርድ ውስጥ በጎዳና ላይ በጉልት ንግድ ይተዳደሩ ለነበሩ እናቶች ዘመናዊ የንግድ ሼድ ሰርተንና አስፈላጊውን ግብዓት ሁሉ አሟልተን አስረክበናል! እነዚህ እናቶች ለረጅም ዓመታት ፀሐይና ብርድ እየተፈራረቀባቸዉ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ጤናቸው እየታወከም ቢሆን ለኑሮ ሲሉ በሜዳ ላይ ጉልት እየቸረቸሩ ልጆቻቸውን ያስተማሩና ቤተሰብ ያስተዳደሩ ብርቱ እናቶች ናቸው! ዛሬ የሚገባቸውን ክብር አግኝተውና ተደስተው በማየታችን እኛም ደስ ብሎናል! በከተማችን በስፋት የተገበርነውን የኮሪደር ልማት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የቀድሞውን የጉሊት ንግድ በማንሳት የገነባነውን ዘመናዊና ደረጃውን የጠበቀ የንግድ ሼድ በዛሬው ዕለት አስረክበናቸዋል! በተጨማሪም የምርት አቅርቦት ችግር እንዳይገጥማቸው ከላፍቶ ገበያ ማዕከል ጋር ዘላቂ የገበያ ትስስር እንዲፈጠር ተደርጓል! የአካባቢው ማህበረሰብም ከዚህ ፅድት ካለ፣ ሰፊ የሚኪና ማቆሚያ ካፍቴሪያ እና በቂ የንፅህና ቤቶች ተሟልቶ ከተገነባለት የገበያ ስፍራ እና ከእነዚህን ጠንካራ እናቶች ምርታቸውን በመሸመት እንድታበረታቷቸው በአደራ ጭምር ጥሪዬን አቀርባለሁ! ልማታችን ሰው ተኮር ነው ስንል ይህ ተግባር አንዱ ማሳያ ነው! ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ