У нас вы можете посмотреть бесплатно ዓላማ መር ህይወት- ቀን 40_Purpose driven Life - Day 40_ alama mer hiywet- ken 40 или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
40ኛዉ ቀን በዓላማ መኖር "በሰው ልብ ብዙ ሐሳብ አለ፤ የሚፈጸመው ግን የእግዚአብሔር ሐሳብ ነው፡፡" ምሳሌ 19-21 "ዳዊት በራሱ ዘመን የእግዚአብሔር ፈቃድ ካገለገለ በኃላ አንቀላፋቶል፡፡" የሐዋ. 13:36 የእርግጠኛ ኑሮ ብቸኛዉ መንገድ ፣በዓላማ መኖር ነዉ፡፡ከዚህ ዉጭ ኑሮ ዝም ብሎ ይሆናል፡፡ ብዙ ሰዎች ከሦስት መሠረታዊ የሕይወት ጉዳዮች ጋር ይታገላል፡፡ የመጀመሪያዉ የማንነት ጉዳይ ነዉ ፤"እኔ ማን ነኝ?" ፤ሁለተኛዉ ጠቃሚ ወይም ተፈላጊ የመሆን ጉዳይ ነዉ "ፋይዳ ያለኝ ሰዉ ነኝን?" ፤ሦስተኛዉ የተጵዕኖ ጉዳይ ነዉ "በሕይወት ዉስጥ ያለኝ ድርሻ ምንድነው ? ፡፡የእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ እግዚአብሔር ለሕይወትህ ባለዉ አምስተኛ ዓላማዎች ዉስጥ ይገኛል ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዝሙርቱ ጋር በመጨረሻዉ ዕለት እግራቸዉን አጠበና ፦"ይህን ብታዉቁ ብታደርጉም ብፁዓን ናችሁ ፡፡" ዮሐ 13:17 አላቸው፡፡ እግዚአብሔር እንድታደርግ የሚፈልገዉን ነገር አንዴ ካወቅህ ፣በረከቱ የሚመጣዉ ያወቅኸዉን ስታደርግ ነዉ፡፡ እንግዲህ አብረን ያደረግነው ይህን የአርባ ቀን ጉዞ ወደ መጨረሱ ስንቃረብ ፣እግዚአብሔር ለሕይወትህ ያለዉን ዓላማዎች አዉቀሃልና በተግባር ላይ ካዋልካቸዉ ትባረካለህ፡፡ አምስቱን የእግዚአብሔር ወሳኝ ዓላማዎች ግን የግድ ልታደርጋቸዉ ይገባል(1 ለምንድነው የተፈጠርኩት ፣ለእግዚአብሔር ደስታ የታቀድክ ነህ ፣የተቤጀኸዉ ለእግዚአብሔር ቤተሰብነት ነዉ ፣ክርስቶስን ለመምስል ነዉ የተፈጠርከዉ ፣የተበጀኸዉ እግዚአብሔርን ለማገልገል ነዉ ፣የተሠራኸዉ ለተልዕኮ ነዉ)፡፡ የሕይወት ዓላማ መገለጫ ምንድነው ?? እግዚአብሔር ለሕይወትህ ያለዉን ዓላማ ባጭሩ የሚገልጥበት ዐረፍተ ነገር ነዉ፡፡ እግዚአብሔር ለሕይወትህ ያለዉን አምስት አላማዎች ለመፈፀም ቃል መግባትህን በራስህ ቃል የምታረጋግጥበት ነዉ፡፡ 👌የዓላማ መገለጫ ፣የግቦች ዝርዝር አይደለም ፡፡ግቦች ጊዜያዊ ሲሆኑ ፣ዓላማ ግን ዘላለማዊ ናቸዉ፡፡ "የእግዚአብሔር ምክር ግን ለዘለዓለም ይኖራል ፥የልቡም ሀሳብ ለልጅ ልጅ ነዉ፡፡" መዝ 33:11 ዓላማዎችህን በወረቀት ላይ ማስፈር በተለይ ስለ ሕይወት አቅጣጫ እንድታስብ ያስገድድሃል፡፡ የሕይወት ዓላማ መገለጫ በገንዘብ ፣በሕይወትህና በጊዜህ ምን እንደምታደርግ መጠቆም ብቻ ሳይሆን ፣ምን ማድረግ እንደማይገባህ ያመለክትሃል፡፡ ስኬት ማለት ላንተ ምን ማለት መሆኑን የሚገልጥ ነዉ፡፡ዓለም ዋነኛ ምትለዉ ሳይሆን አንተ ዋነኛ ነዉየምትለዉን መሆን ነዉ፡፡ "ከሁሉ የሚሻለዉን ለይታችሁ ታዉቁ ዘንድ..."ፊሊ 1:10 በሕይወትህ በየደረጃዉ የተለያዩ ድርሻዎች ቢኖሩህም ዓላማዎችህ ግን የማይቀየሩ ናቸዉ፡፡ የሕይወትህ ዓላማ መገለጫህን ለመፃፍ ጊዜ ዉሰድ፡፡በመጀመሪያ ሙከራህ በአንዴ ቁጭ ብለህ ያለቀለት ነገር በመፃፍ አትሞክር፡፡የመጣልህን አሳብ ወዲያው ፃፈዉ፡፡ምን ጊዜም አዲስ ከመፃፍ የተፃፈዉን ማረም ይቀላል፡፡ የሕይወት ዓላማ መገለጫ ስታዘጋጅ ልብ ልትላቸዉ የሚገቡ ጥያቄዎች አምስቱን እነሆ 1. የሕይወቴ ማዕከል ሊሆን የሚገባዉ ምንድነው ??የምትኖረዉ ለማነዉ/ሕይወትህን ልትገነባ የተዘጋጀኸዉ ለምን ዓላማ ነዉ?የመተዳደሪያ ሙያህን ፣ቤተሰብህን ፣የመዝናኛ ልማድን ፣ገንዘብ ፣ጨዋታንና ሌሎች ተግባራትን የሕይወትህ ማዕከላት ልታዘጋጅ ትችላለህ እነዚህ ሁሉ ነዉጥ በገጠመህ ጊዜ አንተን ደግፎ የሚያቆይ ጥንካሬ የላቸውም ፡፡አንድ የማይናወጥ ማዕከል ያስፈልግሃል፡፡ ✅ እግዚአብሔር የሕይወትህ ማዕከል ሲሆን ታመልከዋለህ፡፡ባልሆነ ጊዜ ደግሞ ትጨነቃለህ፡፡ ጭንቀት እግዚአብሔር በሕይወትህ ወደ ጥግ ገፋ የተደረገ መሆኑ የሚያስጠነቅቅ ምልክት ነዉ፡፡መልሰህ የሕይወትህ ማዕከል ስታደርገዉ ግን ወዲያው በደስታ ትሞላለህ፡፡ 2. የሕይወቴ ባህሪይ ምን መሆን ይኖርበታል ?? ይህ ደቀመዝሙርነትን የሚጠይቅ ጥያቄ ነዉ፡፡ ምን አይነት ሰዉ ነዉ የምትሆነዉ??እግዚአብሔር የሚገደዉ ፣ከምታደርገዉ ነገር ይልቅ የምትሆነዉን ነዉ፡፡ ልብ በል አብሮህ የሚቆየዉ ባህሪይ እንጂ የመኖሪያ ሙያህ አይደለም፡፡ ገላ 5:22፣ ማቲ. 5-7 የክርስቶስን የመሰለ ባህሪይ ለማዳበር የሚደረገዉ ጥረት የዕድሜ ልክ ጉዳይ ነዉ፡፡ 3. ከሕይወቴ የሚጠብቀው ድርሻ ምን ሊሆን ይገባል ?? ይህ ለማያምን ሰዎች የሚኖርህን አገልግሎት የሚመለከት ጥያቄ ነዉ?? 4. ህይወቴ ሊያስተላልፍ የሚገባ መልዕክት ምንድነው?? አማኝ ያልሆኑ ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ተዓማኒነት ከመቀበላቸዉ በፊት ፣የሕይወታችንን ተዓማኒነት ለማወቅ ይፈልጋሉ፡፡ 5. በሕይወቴ ልቀላቀለዉ የሚገባ ማህበረሰብ የቱ ነዉ? ይህ ደግሞ ህብረትን ይጠይቃል፡፡ለሌሎች አማኞች ለእግዚአብሔር ቤተሰቦች ያለህ ቃል ኪዳንና ግንኙነት እንዴት ትገልጠዋለህ?? ምናልባት "እግዚአብሔር ለስራዬ ለትዳሬ ለምኖርለትና ለምማረክበት ቦታ ያለዉ ፈቃድ ምንድነዉ?? ✅ለዘላለም የሚዘልቀዉ እግዚአብሔር ለሕይወትህ ያለዉ ዓላማ ስለሆነ በራስህ ሳይሆን በእርሱ ዕቅድ ላይ አተኩር፡፡ እግዚአብሔር ሊጠቀምብህ ይፈልጋል የዛሬ ሠላሳ ዓመት ገደማ የሕይወቴን አቅጣጫ ለዘላለም ያስለወጠኝን አንድ ቃል "ዳዊት በራሱ ዘመን የእግዚአብሔር ፈቃድ ካገለገለ በኃላ አንቀላፋ" "እንደ ልቤ የሆነ ፈቃዴን የሚያደርግ... የሐዋ. 13:36 ከዚህ የሚበልጥ ታላቅ የመታሰቢያ ፅሁፍ የለም፡፡ በዓላማ መኖር ዛሬ ልትጀምር ትችላለህ ፡፡ ጳዉሎስ በዓላማ የሚመራ ሕይወት ነዉ የኖረዉ "ለእኔ መኖር ክርስቶስ ነዉ ፤ሞትም ማትረፍ ነዉ"ፊል 1:21 ሞትንም ሆነ ኑሮን አልፈራም ፡፡ በሁለቱም መንገድ የእግዚአብሔር ዓላማ ይፈፀማል፤ በፍፁም አይከስርም፡፡ ስለዕቅዱ እናመሰግንዋለን፤ ለዓላማው ለዘላለም እንኖራለን፡፡ 🔔አላማ መር ህይወት ለመኖር ምን ማቆምና ምን ለማድረግ እርምጃ መጀመር አለብኝ ??? በሪክ ዋረን አላማ መር ህይወት