У нас вы можете посмотреть бесплатно 8ኛ ትምህርት :- በፊልጵስዩስ እና በቆላስይስ - ኢየሱስ ከሁሉም ነገር የመጀመሪያውና ዋነኛው или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ለዚህ ሳምንት ጥናት የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡ፡- ዘፍ. 1:26, 27፣ ቆላ. 1:15–18፣ ኤፌ. 1:22። የመታሰቢያ ጥቅስ፡ “እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው። የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኵር ነው። ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል። እርሱም ከሁሉ በፊት ነው ሁሉም በእርሱ ተጋጥሞአል” (ቆላ. 1:15–17)፡፡ በዚህ ሳምንት ጳውሎስ ለቆላስይስ ሰዎች የጻፈውን መልእክት ማጥናት እንጀምራለን። ስለ ቆላስይስ ሰዎች በ1ኛ ትምህርት እና 2 ላይ አስቀድመን በጥቂቱ ተመልክተናል። በ2ኛ ትምህርት የሀሙሱ ጥናት ላይ ጳውሎስ በቆላስይስ ከተማ ላሉ ክርስቲያኖች ይጸልይ እንደነበር አይተናል (ቆላ. 1፡9-12)። በቁጥር 12 እና 13 ላይ ጳውሎስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ከሰይጣን መንግሥት ጋር ያነጻጽረዋል። የእግዚአብሔር መንግሥት በብርሃን ሲመሰል የሰይጣን መንግሥት ደግሞ በጨለማ ተመስሏል። እግዚአብሔር ከሰይጣን ኃይል አድኖናል። የመንግስቱም ዜጎች አድርጎናል። እግዚአብሔር አብ ስለ ኢየሱስ ሲል ኃጢአታችንን ይቅር ይለናል (ቆላ. 1፡13, 14)። ኢየሱስ አምላካችን ነው። እርሱ ፈጠረን። ራሱም ያድነናል። በኢየሱስ ስናምን፣ እግዚአብሔር ከሰይጣን መንግሥት ያፈልሰናል፤ የሰማይም ዜጎች ያደርገናል። እግዚአብሔር እነዚህን ነገሮች ያደረገልን፣ ኢየሱስ እኛን ለማዳን በሠራው ሥራ ነው። በዚህ ሳምንት ጳውሎስ ለቆላስይስ ሰዎች በጻፈው መልዕክት ውስጥ ስለ ኢየሱስ የተናገራቸውን አንዳንድ ነገሮች እንመለከታለን። እነዚህ ጥቅሶች በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ኢየሱስ ከተነገሩት እጅግ ውብ ቃላት መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።