У нас вы можете посмотреть бесплатно 1ኛ ትምህርት :- ኢያሱ - “ለስኬት የሚያበቁ ግብዓቶች” или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ለዚህ ሳምንት ጥናት የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡ፦ ዘዳ. 18፡15-22፣ ኢያሱ 1፣ ዕብ. 6፡17-18፣ ኤፌ. 6፡10-18፣ መዝ. 1፡1-3፣ ሮሜ 3፡31። የመታሰቢያ ጥቅስ፡ ነገር ግን ጽና፥ እጅግ በርታ፤ ባሪያዬ ሙሴ ያዘዘህን ሕግ ሁሉ ጠብቅ፥ አድርገውም፤ በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል። (ኢያሱ 1፡7) የቦስተን ፊልሐርሞኒክ ኦርኬስትራ የሙዚቀ ዳይሬክተር የሆነው ቤንጃሚን ዛንደር የሙዚቃ ትርጉም ክፍለ ጊዜን ያስተምራል። ብቃታቸው በሚፈተሽበት ጊዜ የተማሪዎቹን ጭንቀት ይመለከት ስለነበር ተማሪዎቹ እንዳይጨናነቁ እና ሙሉ አቅማቸውን መጠቀም እንዲችሉ በመጀመሪያው ክፍለ ጊዜ ሁሉም ሰው ኤ እንደሚያገኝ ነገራቸው። ይህ ኤ ግን ዝም ብለው የሚጠብቁት ሳይሆን ለማግኘት በመስራት ውስጥ የሚሳካ ነበር። ብቸኛው ቅድመ ሁኔታ ተማሪዎቹ በሴሚስተሩ የመጀመሪያ ሁለት ሳምንታት ውስጥ የደብዳቤውን ቀን የትምህርቱ መጨረሻ ቀን አድርገው ደብዳቤ መፃፍ ነበር። ደብዳቤው ለምን ያ ከፍ ያለ ውጤት እንደሚገባቸው መግለፅ ነበረበት። የኢያሱ መጽሐፍ የሚናገረው ስለ አዲስ ጅማሮዎች እና አዲስ ውጤቶች ነው። የእስራኤልን ታሪክ 40 ዓመታት የመራው ሙሴ አሁን ያለፈ ታሪክ ነበር። በሚያሳዝን ሁኔታ በአመፅ እና በአንገተ ደንዳናነት የሚታወቀው ከግብጽ የመውጣትና በበረሃ የመንከራተት ዘመን አብቅቷል። እግዚአብሔርን ለመታዘዝ ፈቃደኛ የሆነው አዲሱ ትውልድ፣ እንዲሆን በተስፋ እንደሚጠብቅ ሳይሆን በውስጡ እንደሚኖር ሕዝብ፣ ወደ ተስፋይቱ ምድር ለመግባት ተዘጋጅቶ ነበር።፡