У нас вы можете посмотреть бесплатно ሰርዴስ ክፍል 1 | ሰባቱ አብያተክርስቲያናት | ፓስተር አስፋው በቀለ | www.operationezra.com или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ሰርዴስ፡ ሞተው ሳሉ በሕይወት አለን ብለው የሚያስቡ አማኞች (ራእይ 3፡1-6)። የሰርዴስ ከተማ በአንድ ወቅት ሀብታም የነበረች ስትሆን፥ የቀድሞው የሊዲያ መንግሥት ርእሰ ከተማ ነበርች። ከተማይቱ የተገነባችው በኮረብታ ላይ ሲሆን፥ በታላቅ ቅጥር የተከበበች ነበረች። ነዋሪዎቿ ማንም ይህችን ከተማ ሊወራት እንደማይችል ያስቡ ነበር። ነገር ግን ትዕቢታቸውና ልበ ሙሉነታቸው ለሽንፈት ዳረጋቸው። ከተማይቱ ቀስ በቀስ እየፈራረሰች የነበረች ቢሆንም እንኳ፥ እነርሱ ግን ስለ ቀድሞ ክብሯ እየተናገሩ ይታበዩ ነበር። የሚያሳዝነው ቤተ ክርስቲያኒቷም የእነርሱን ምሳሌነት መከተል ጀመረች። አማኞች በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ጤናማ እንደሆኑ በማሰብ በቀድሞ ታላቅነታቸው ይመኩ ጀመር። በእግዚአብሔር ዓይኖች ፊት ግን ሙታን ነበሩ። ምክንያቱም ምግባረ ብልሹነት ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዲገባ አድርገው ነበር። ክርስቶስ በአንድ ወቅት ታላቅ በነበረችው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጥቂት ታማኞች እንደነበሩ ያውቅ ነበር። ስለሆነም እነዚህ አማኞች ሕይወታቸውን እንዲመረምሩና ንስሐ ገብተው ባሕርያቸውን እና ተግባራቸውን እንዲለውጡ ያስጠነቅቃቸዋል። ይህ ካልሆነ ግን ክርስቶስ እንደ ሌባ መጥቶ እንደሚፈርድባቸው ይናገራል። ይህም ከብዙ ዓመታት በፊት የፋርስ ሠራዊት ከተማቸውን ከደመሰሱበት ሁኔታ ጋር ይመሳሰል ነበር። ክርስቶስ ታማኞችና ንጹሐን ሆነው የሚጸኑ አማኞች ግን ከእርሱ ጋር ነጭ ልብስ ለብሰው እንደሚሄዱ ይናገራል። በዮሐንስ ራእይ ውስጥ ነጭ ልብስ የዳኑትን፥ የተከበሩትን፥ እንዲሁም ከዓለም ቆሻሻና ክፋት ነፃ የወጡትን አማኞች ያመለክታል። እነዚህ ሰዎች ከተማቸው ከሚታወቅበት አልባሳት የላቁ ሌሎች ልብሶችን ይጎናጸፋሉ። ስማቸውም ከሕይወት መጽሐፍ አይደመሰስም። በጥንት ዘመን የዜጎች ስሞች በትልቅ መጽሐፍ ውስጥ ይመዘገብ ነበር። ነገር ግን አንድ ሰው በራሱ ወይንም በሚኖርበት ከተማ ላይ አሳፋሪ ተግባር ከፈጸመ፥ የከተማይቱ መሪዎች የግለሰቡን ስም ይሰርዙ ነበር። የክርስቶስ ተከታዮች ዓለምን በመምሰል የክርስቶስን ስም ካሰደቡ ስማቸውን ከመንግሥተ ሰማይ ዜጎች ስም ውስጥ እንደሚሰርዝ ያስጠነቅቃል። ንጹሐን ሆነው ካልኖሩ በሰማይ ክርስቶስ እውቅናን እንደማይሰጣቸው ይናገራል። እርሱ «ይህ ልጄ ነው የመንግሥተ ሰማይ አባል ነው» ሲል አይመሰክርም።