У нас вы можете посмотреть бесплатно ፍርድ ቤቱ ለጆሲ ወሰነ|እናት ልጇን በመነጠቋ ሆስፒታል መግባቷን ገለፀች( или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ድምፃዊ ዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ) እና በቀድሞ ፍቅረኛው መካከል የነበረው የልጅ አስተዳደግ ክርክር በድምፃዊው አሸናፊነት ተጠናቀቀ የቀድሞ የድምፃዊ ዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ ኢን ዘ ሃውስ) የፍቅር ጓደኛ ሶሲ ግርማይ ለስድስት ወራት ያህል በፍርድ ቤት ሲካሄድ የቆየው የልጅ አስተዳደግ ክርክር በድምፃዊው አሸናፊነት መጠናቀቁን በምሬት ገለጸች። ሶሲ በፌስቡክ ገጿ ባሰፈረችው መልዕክት የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከእናትነት ፍቅር ይልቅ ቁሳዊ ነገሮችን መሠረት ያደረገ ነው ስትል ወቅሳለች። የክሱ መነሻና የምስክሮች ቃል በክርክሩ ወቅት ድምፃዊው በሶሲ ላይ "በምሽት ክበብ ትሰራለች፣ ሱሰኛ ነች፣ ልጁን ለገንዘብ መጠየቂያ ታደርጋለች" የሚሉ ክሶችን አቅርቦ እንደነበር ሶሲ ገልጻለች። ሆኖም ግን ሶሲ ስራዋ የባልትና ውጤቶችን ማቅረብ መሆኑን ምንም አይነት ሱስ እንደሌለባትና ለልጆቿ መልካም እናት መሆኗን ጎረቤቶቿና ቤተሰቦቿ ምስክርነት በመስጠት ክሱን ማስተባበላቸውን አስረድታለች። በተቃራኒው ድምፃዊው ዮሴፍ ገብሬ ልጁ ባለበት ተገቢ ያልሆኑ ሱሶችን እንደሚጠቀምና የልጁን የትምህርት ቤት ክፍያ እንኳን እንደማይከፍል በማስረጃ ማረጋገጧን ገልጻለች። እንደ ሶሲ ገለፃ ጉዳዩን የመረመሩት የሶሻል ወርከሮች (ማህበራዊ ሰራተኞች) ያቀረቡት ሪፖርት ለውሳኔው ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ሪፖርቱ በዋናነት ትኩረት ያደረገው በሁለቱ ወገኖች የኑሮ ደረጃ ላይ ሲሆን፦ የድምፃዊው ገቢ ከእሷ የተሻለ መሆኑ፣ ቤቱ ሰፊና ለልጁ የተለየ መኝታ ቤት ያለው መሆኑ፣ መኖሪያው ቦሌ አካባቢ መሆኑና ለልጁ መጫወቻዎች መኖራቸውን መሠረት በማድረግ ልጁ ከአባቱ ጋር እንዲያድግ ወስነዋል። በዚህም መሠረት ፍርድ ቤቱ ልጁ ከአባቱ ጋር እንዲኖር የወሰነ ሲሆን እናትየው በየሁለት ሳምንቱ አንድ ቀን ብቻ (እሁድ ለጥቂት ሰዓታት) እንድትጎበኝ ተፈቅዶላታል። ሶሲ በሰጠችው አስተያየት "ከቁስ ከቤትና ከመኪና እናትነት እንደሚያንስ ሲነገርህ እንደማዘን ሰባሪ ነገር የለም" በማለት ጥልቅ ሀዘኗን ገልጻለች። ምንም እንኳን ጠበቃዋ ሰብለ አሰፋ አስፈላጊውን ማስረጃ ሁሉ አቅርባ የተከራከረች ቢሆንም ውጤቱ ግን እናትነትን የገፋ ነው ስትል አማራለች። በመጨረሻም በአሁኑ ሰዓት በሆስፒታል እንደምትገኝ የገለጸችው ሶሲ"ሀቄን ከፈጣሪ እጠብቃለሁ" ስትል መልዕክቷን ደምድማለች። ድምፃዊ ዮሴፍ ገብሬ በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጠው ምላሽ የለም።