У нас вы можете посмотреть бесплатно እናት በጭንቅት ልትሞት ነው|አባት የሚሆነው ነገር ጠፍቶታል|ከታገተ 25 ቀናት ሆኑት የዓመት ከ6 ወር የሆነው ልጃቸው ድመፁ ጠፍቷል(@gizemedia1974) или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
የቤተሰብ ድምፅ - ሰሜን ሸዋ፣ ደራ በአሁኑ ሰዓት የብዙዎችን ልብ የነካውና በታላቅ ጭንቀት ውስጥ የሚገኘው የጤና ባለሙያው አቶ ፍስሀ እና የባለቤታቸው መቅደስ ታሪክ፣ ሁላችንም በጸሎትና በጋራ ርብርብ እንድንቆም ጥሪ ያቀርባል። የ 1 ዓመት ከ 6 ወር ጨቅላው ህፃን ፍፁም ፍስሀ፣ ከእናቱ እቅፍ ከተለየ 23 ቀናት ተቆጥረዋል። ባለፈው ጥር 27 ቀን፣ እናት መቅደስ ሁለት ህፃናት ልጆቿን ይዛ ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ ለለቅሶ በምትጓዝበት ወቅት፣ ባጋጠመው ያልተጠበቀ እገታ ምክንያት ከትንሽ ልጇ ጋር ለመለያየት ተገድዳለች። እናትና ትልቁ የ 5 ዓመት ልጇ በድካም ምክንያት በረሃ ላይ ወድቀው በሚሊሻዎች ተገኝተው ቢተርፉም፣ ትንሹ ፍፁሜ ግን እስካሁን ያለበት አልታወቀም። አባት አቶ ፍስሀ ልጁን ለማግኘትና ወደ እናቱ እቅፍ ለመመለስ ያልሞከረው ሙከራ የለም። ልጄ የት ነው ያለው? *ምን ይበላ ይሆን?" የሚለው ጥያቄ ቤተሰቡን ለከፍተኛ ስቃይ ዳርጎታል። አሁንም ተስፋቸውን በፈጣሪና በኢትዮጵያ ህዝብ ትብብር ላይ አድርገዋል። ይህ ታሪክ የሁላችንም የቤት ስራ ነው። ፌስቡክን የምንጠቀመው ለእንዲህ ያለ በጎ ተግባር መሆን አለበት። ይህ ጽሁፍ የታለመው ህፃኑን ያዩ ሰዎች ካሉ ጥቆማ እንዲሰጡና ቤተሰቡን ከጭንቀት ለመታደግ ነው። ሰብአዊነት፡ ማንኛውም ጨቅላ ህፃን ከእናቱ ጡት መራቅ የለበትም። ዛሬ ለዚህ ህፃን ድምፅ በመሆን አጋርነታችንን እናሳይ። መረጃውን በስፋት በማጋራት (Share በማድረግ) ለደራ ወረዳና ለአካባቢው ነዋሪዎች እንዲደርስ እናድርግ። ህፃኑ ያለበትን ፍንጭ ለሚያውቅ ወይም ላየ ሰው በሚከተሉት ስልኮች እንዲያሳውቁ ቤተሰቡ በትህትና ይጠይቃሉ፡- 0942749747 0909076440 "መልካምነት ለራስ ነው - ሼር በማድረግ ተባበሩ!(@gizemedia1974)