У нас вы можете посмотреть бесплатно በክልሉ የታቀደውን የምርት ጭማሪ ለማሳካት የድህረ ምርት ብክነትን መቀነስ የሚያስችሉ የቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎችን መተግበር እንደሚያስፈልግ ተገለፀ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
በክልሉ የታቀደውን የምርት ጭማሪ ለማሳካት የድህረ-ምርት ብክነትን መቀነስ የሚያስችሉ የቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎችን መተግበር እንደሚያስፈልግ ተገለፀ በአማራ ክልል የ2017/18 የመኸር ምርት ዘመን የደረሱ ሰብሎችን የመሰብሰብ ስራ ተጀምሯል። በክልሉ በምርት ዘመኑ ከ5 ሚሊዮን በላይ ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል። በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች የደረሱ ሰብሎችን የተለያዩ ዘመናዊ የምርት መሰብሰቢያ ማሽነሪዎችን በመጠቀም ምርት እየተሰበሰበ ይገኛል ያሉት የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ማንደፍሮ አስላከ ይህም ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ነው ያሉት። እስካሁንም 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የተዘራው ምርት ተሰብስቧል ነው ያሉት። እንደ ክልል በሁሉም አካባቢዎች እየታየ ያለው የሰብል ቁመና የተቀመጠውን የምርትና ምርታማነት ጭማሪ ሊያሳካ በሚችል ሁኔታ ላይ ይገኛል። የተቀመጠውን ግብ ሙሉ ለሙሉ ለማሳካት ደግሞ አርሶአደሮች የድህረ-ምርት ብክነትን መቀነስ የሚያስችሉ ቅድመ-ጥንቃቄ እርምጃዎችንም በትክክል በመተግበር ሰብሉ ያለምንም ብክነት ተሰብስቦ በጥንቃቄ ወደ ጎተራ መግባት አለበት ሲሉ ዳይሬክተሩ አሳስበዋል። በክልሉ በምርት ዘመኑ የታቀደውን 187 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማሳካት አርሶ አደሮች፣ የግብርና ባለሙያዎች እና አመራሮች በጋራ ተቀናጅተው የሰብል ስብሰባ ስራውን በባሕላዊ ዘዴ እና የተሻሻሉ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንዲያከናውኑ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ ዶ/ር ማንደፍሮ አስላከ መልዕክት አስተላልፈዋል።