У нас вы можете посмотреть бесплатно የየካቲት 1 ሥንክሳር или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት 1 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተባረከ የየካቲት ወርመዓልቱ ዐሥራ አንድ ሰዓት ነው ከእንግዲህም ይጨምራል በዚችም በየካቲት አንድ የከበሩ የመቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ በቍስጥንጥንያ ከተማ በታላቁ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት ተደረገ ። ስብሰባቸውም የሆነው በቍስጥንጥንያ አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት ስለ ሆነው የክብርባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን በከፋች ኀሳቡ ፍጡር ነው ብሎ ስለ ካደው ስለ መቅዶንዮስ ሁለተኛም አንድ ገጽ ስለሚሉ ስለ ሰባልዮሳውያን ሦስተኛ ወልድ ከብቻው ሥጋ በቀር ነባቢት ለባዊት ነፍስን አልነሣም መለኮቱ በነፍስና በልቡና ፈንታ ሆነው ስለሚሉ ስለ አቡሊናርዮሳውያን ነው ። የእሊህ ከሀድያንም ስሕተት ግልጽ በሆነ ጊዜ አሰባስቦ የአንድነት ጉባኤ ያደርግላቸው ዘንድ ንጉሥ ቴዎዶስዮስን ለመኑት እርሱም ቃላቸውን ተቀብሎ ወደ ሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ኢየሩሳሌምም ኤጲስቆጶስ ወደ እስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳትም መልእክትን ላከ ምሁራን የሆኑ ኤጲስቆጶሶቻቸውንም ይዘው እንዲመጡ አዘዛቸው ። እሊህም አባቶች በቍሰጥንጥንያ ከተማ ተሰበሰቡ የሮሜው ሊቀ ጳጳሳት ግን አልመጣም ምሁራን የሆኑ ሰዎችን ላከ እንጂ ከእሳቸውም ጋር በእጁ የጻፉትን ደብዳቤ ላከ ። የጉባኤውም ሊቀ መንበር የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ ነው መቅዶንዮስንም ጠርቶ የረከሰች ሃይማኖቱን ይናገር ዘንድ አዘዘው ያ ከሀዲም እንደ ፍጥረቶች ሁሉ መንፈስ ቅዱስ የተፈጠረ ነው አለ ። ጢሞቴዎስም መልሶ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሕይወቱ እንደሆነ አታውቅምን የእግዚአብሔርን ሕይወት እንዴት ፍጡር ታደርገዋለህ አሁንም ከዚች ከረከሰች ሃይማኖትህ ተመለስ ወደ ዘላለማዊ እሳተ ገሃነም ከመግባትህ በፊት ንስሓ ግባ አለው ። እርሱ ግን ሰምቶ አልተመለሰም እነርሱም አወገዙት ከሹመቱም ሻሩት ከቤተ ክርስቲያንም አሳደዱት ። ከዚህም በኋላ ሰባልዮሳውያንን ጠርቶ እናንተስ ስለ ሃይማኖታችሁ ምን ትላላችሁ ተናገሩ አላቸው እነርሱም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ገጽ አንድ ህላዌ ነው በምንም በምን ሦስት አይሆንም አሉ ። አባት ጢሞቴዎስም መልሶ እንዲህ አላቸው በዮርዳኖስ ውስጥ ወልድ ቁሞ ሳለ በፀዓዳ ርግብ አምሳል መንፈስ ቅዱስ ወርዶ በራሱ ላይ ተቀመጠ አብም ከደመና ውስጥ ሁኖ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ አሰምቶ ተናገረ ያለው የወንጌል ቃል ተሻረን ። እናንተ እንደምትሉት ከሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቃችሁት የክርስትናችሁ ጥምቀት ተሽሮአል አሁንም ክህደታችሁን ተዉ ብትመለሱም ይሻላችኋል ። አርዮስም አስቀድሞ ወልድን ካደው ይህ መቅዶንዮስም መንፈስ ቅዱስን ካደው እናንተም የእነርሱ ተሳታፊዎች ሆናችሁ ። እነርሱም ሰምተው አልተመለሱም የአንድነት ጉባኤም አውግዞ ከምእመናን አንድነት ለያቸው ። ከዚህም በኋላ ደግሞ ወልድ ነባቢት ለባዊት የሆነች ነፍስን አልነሣም ሥጋን ብቻ እንጂ የሚለውን የአቡሊናርዮስን ትምህርት አወገዙ ። እሊህ መቶ ኃምሳ የሆኑ ኤጲስ ቆጶሳት አባቶቻችንም በጸሎተ ሃይማኖት ላይ ጌታ አዳኝ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋራ በነቢያት አድሮ የተናገረ የሚለውን ጨመሩ ። ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን ። ኃጢአትን ለማስተሰረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን ። የሙታንንም መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ ተስፋ እናደርጋለን ። ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱ አባቶቻችን የተናገሩት ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እስከሚል ነው ። እሊህ መቶ ኃምሳው አባቶች የተሰበሰቡት ስለ መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ስለርሱ የእርሱን ነገር አብራሩ ። ለእርሱም ምስጋና ይሁን የአባቶቻችንም በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። ቅዱስ ጴጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት በዚችም ዕለት በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ መንግሥት ፍጻሜ በሰማዕትነት የሞተ ከሀዲ አርዮስንም ያወገዘ የሰማዕታትም ፍጻሜ የሆነ የሊቀ ጳጳሳት የቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት ነው ። ጻድቁ ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ የጣዖታትን ቤቶች ሁሉ አፈረሰ ይችንም ቤተ ክርስቲያን ከእስክንድርያ ከተማ በምዕራብ በኩል በቅዱስ ጴጥሮስ ስም አነፃት በዛሬዋም ዕለት ከበረች በውስጧም ብዙ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ። ያቺም ቤተ ክርስቲያን እስላሞች በግብጽ እስከ ነገሡበት ዘመን ኖረች ከዚያም በኋላ ቢሆን የታወቀች ሁና ትኖር ነበር ከዚህም በኋላ ፈረሰችና ምድረ በዳ ሆነች ። የቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን ግን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እጅ የተያዘችና የተጠበቀች ናት ።ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን ። የካቲት ፩ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፪.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዳሴ ቤቱ ፫.ታላቁ ቴዎዶስዮስ ጻድቅ ንጉሠ ቍስጥንጥንያ ወርኀዊ በዓላት ፩.ልደታ ለቅድስት ድንግል ማርያም እግዝእትነ ፪.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ ፫.ቅዱስ ሚልኪ ቁልዝማዊ ፬.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት ፭.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ስለዚህ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያንን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ዻዻሳት አድርጎ ለሾመባት: ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ : ከሄድሁ በሁዋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ እኔ አውቃለሁ: ስለዚህ ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሰጽ እንዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ ። ሐዋ. ፳፥፳፰ @Fewus_Menfesawi_Aba_Gebrekidan @EfoyZeOrthodox @yekidusantarik