У нас вы можете посмотреть бесплатно የየካቲት 4 ሥንክሳር или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት 4 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት አራት በዚች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሐዋርያ የከበረ አጋቦስ በሰማዕትነት ሞተ ። ይህም ቅዱስ ጌታችን ከመረጣቸውና ይሰብኩ ዘንድ ከመከራው በፊት ከላካቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ ነው በጽርሐ ጽዮንም አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋር ስጦታውን ተቀብሏል ። እግዚአብሔርም የትንቢትን ሀብት ሰጠው ስለርሱ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እንደ ተናገረ የቅዱስ ጳውሎስን መታጠቂያ አንሥቶ ራሱ እግሮቹን አሠረባትና የዚችን መታጠቂያ ባለቤት በኢየሩሳሌም አይሁድ እንዲህ ያሠሩታል አለ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ትንቢት ተናገረ ትንቢቱም ተፈጸመች ። ከዚህም በኋላ ሕይወት በሆነ በወንጌል ትምህርት ሊአስተምር ከሐዋርያት ጋር ወጣ እያስተማረና ቀና የሆነ የእግዚአብሔርን መንገድ እየመራ ብዙ አገሮችን ዞረ ከአይሁድና ከዮናናውያንም ብዙዎችን የክብር ባለቤት ወደሆነ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅን ሃይማኖት አስገባቸው በከበረች በክርስትና ጥምቀትም አነፃቸው ። ቅናትን የተመሉ አይሁድም ብቻውን በኢየሩሳሌም በድንገት ያዙትና ታላቅ ግርፋትንም ገረፉት ከዚህም በኋላ በአንገቱ ገመድ አስገብተው እስከ ከተማ ውጭ ጐትተው በዚያም ነፍሱን እስከአሳለፈ ድረስ በደንጊያ ወገሩት ። በዚያንም ጊዜ ከሰማይ ብርሃን ወርዶ በሥጋው ላይ እንደ ምሰሶ ተተከለ ወደ ሰማይም ደርሶ አሕዛብ ሁሉ ወደርሱ ሲመለከቱ ነበር ። እግዚአብሔርም የአንዲት አይሁዳዊት ሴት ልቡናዋን ገለጠላት እርሷም በውስጥዋ ሽንገላና ቅናት ጠብ የሌለባት ናት የኦሪትንም ሕግ የምትጠብቅ ነበረች እርሷም ይህን ብርሃን አይታ ይህ ሰው እውነተኛ ነው አለች ። ያን ጊዜም በላይዋ ብርሃን ወረደ እንዲህ ብላ ጮኸች እኔ በቅዱስ አጋቦስ ፈጣሪ የእግዚአብሔር ልጅ በሆነ በጌታ ኢየሱስ የማምን ክርስቲያን ነኝ እግዚአብሔርንም ከፍ ከፍ እያደረገች ስታመሰግነው በደንጊያ ወገሩዋት ነፍሷንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠች ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋርትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ቀን በምግባር ፍጹም የሆነ ተጋድሎውም የበዛ አባ ዘካርያስ አረፈ እርሱንም ነፍሱ ከሥጋው በምትለይ ጊዜ አባ ሙሴ ወንድሜ ሆይ ምን ታያለህ አለው እርሱም ለእኔስ ዝምታ ይሻለኛል አለ ነፍሱም ስትወጣ አባ ኤስድሮስ ሰማይ ተከፍቶ አየ ልጄ ዘካርያስ ሆይየመንግሥተ ሰማያት በር ተከፍቶልሃልና ደስ ይበልህ አለው በእንዲህም ያለ ሁኔታ አረፈ ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን ። የካቲት ፬ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩. ሐዋርያው አጋቦስ ፪. አባ ዘካርያስ ወርኀዊ በዓላት ፩.ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ፪.አባ መቃርዮስ ፫.አባ አብርሐ ስለዚህ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያንን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት: ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ : ከሄድሁ በሁዋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ እኔ አውቃለሁ: ስለዚህ ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሰጽ እንዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ ። ሐዋ. ፳፥፳፰ @Fewus_Menfesawi_Aba_Gebrekidan @EfoyZeOrthodox @yekidusantarik