У нас вы можете посмотреть бесплатно አገሩ የዘነጋችው የካራማራው ጀግና፤ አሊ በርኪ | Ali Berki | Karamara | Ethiopia или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
የተከበራችሁ ተመልካቾቻችን ሻለቃ ዓሊ በርኬ ለአገራችን ያበረከቱትን ውለታ አስባችሁ አሁን የሚገኙበትን ወቅታዊ የኑሮ ሁኔታ ተመልክታችሁ የአቅማችሁን ድጋፍ ልታደርጉላቸው እንደምትፈልጉ ገልጻችሁልናል። ለዚህ ኢትዮጵያዊ ክብር ወዳድነታችሁ ያለንን አክብሮት እየገለጽን አድራሻችሁን በገጻችን facebook.com/andafta ብታስቀምጡልን ከሻለቃ ዓሊ በርኬ ጋር ልናገናኛችሁ እንደምንችል እናሳውቃለን። እናመሰግናለን!! ~~~~~~~~~~~~••••••••~~~~~~~~~~~~~~~ አገሩ የዘነጋችው የካራማራው ጀግና፤ አሊ በርኪ ሰላም ጤና ይስጥልን ተመልካቾቻችን ተስፋፊው መሃመድ ዚያድ ባሬ የሚባሉት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት በኢትዮጵያ ላይ ይፋዊ ወረራ የጀመሩት የዛሬ 42 ዓመት በሰኔ ወር 1969 ዓ.ም ነበር፡፡ በወቅቱ ከንጉሳዊ አስተዳደር ውድቀት በኋላ ገና የመንግስትነት ቁመና ላይ ያልደረሰው የደርግ መንግስት በሰሜን ከህወሓት እና ሻዕቢያ፣ በመሃል አገር ከኢህአፓ እንዲሁም በምዕራብ በኩል መጠኑ አነስተኛ ይሁን እንጂ ከኦነግ ጋር ፍልሚያ ላይ ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ ብዙም ወታደራዊ አቅሙ ያልጎለበተው የደርግ መንግስት ከሰይድ ባሬ የገጠመውን ወረራ ተከትሎ በመላው አገሪቱ የእናት አገር ጥሪ መልዕክት አስተላለፈ፡፡ በወቅቱ ከ300 ሺህ በላይ ወጣቶች የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ለስልጠና በታጠቅ ጦር ሰፈር ከተሙ፡፡ የሶማሊያ ጦርነት ሲነሳ በብዙሃኑ ዘንድ ቀድሞ የሚታወሰው ደግሞ በእጅ ቦንብና በክላሽንኮቭ ጠብመንጃ ብቻ የጠላትን ጦር መሪዎች ከእነ ታንካቸው ዶግ አመድ ያደርጉ የነበሩት የያኔው 50 ዓለቃ፤ በኋላም የአገሪቱን ከፍተኛ ወታደራዊ ኒሻን ከኮሎኔል መንግስቱ እጅ የተሸለሙትና አሁን በቀን ስራ ህይወታቸውን የሚገፉት ሻለቃ ባሻ ዓሊ በርኬ ናቸው፡፡ ወታደራዊ መንግስት ስልጣኑን ለህወሓት ኢህአዴግ አስረክቦ ከወጣ በኋላ የመጀመሪያው ዙር ሚሊሻ ዘማቾች አባል የነበሩት ሻለቃ ባሻ ዓሊ በርኬም ለስደት ተዳርገው በኬንያ ስደተኞች ካምፕ ተጠልለው ቆይተዋል፡፡ ወደ ኬኒያ በሚሰደዱበት ወቅት ከኢትዮጵያ ድንበር ሲደርሱ አፈር ዘግነው በመሃረብ ቋጥረው ኬኒያ የገቡት ሻለቃ ዓሊ፤ በማያውቁት ምክንያት ለዘጠኝ ዓመታት በቃሊቲና ዓለም በቃኝ እስር ቤቶች ክስ ሳይመሰረትባቸው ማቀዋል፡፡ ከእስር ቤት ከተፈቱ በኋላ ኑሮን በጎዳናና በቀን ስራ የገፉት ሻለቃ ዓሊ በርኬ ‹‹የወቅቱ የአገራችን የቁርጥ ቀን ልጅ›› የሚሉትን ታማኝ በየነን ሲያደንቁት ቃላት ያጥራቸዋል ቢባል ይቀላል፡፡ ለአጼ ቴዎድሮስ፣ ለደጃዝማች በላይ ዘለቀና ለኮሎኔል አብዲሳ አጋ ያላቸው አክብሮት ከፍተኛ የሆነው ፤እኒሁ የጦር ሜዳ ጀግና፤ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማሪያም አምባገነን ቢሆንም አገሩን የሚወድ ሰው ነበር ይላሉ፡፡ አቶ መለስና ፓርቲያቸው ህወሓት ደግሞ ‹‹የኢትዮጵያ አፍራሾች ናቸው›› ይላሉ፡፡ አሁን የተፈጠረው ለውጥ የህዝብ ድጋፍ ያስፈልገዋል የሚሉት ሻለቃ ዓሊ በርኬ፤ ትውልድና እድገታቸው ወለጋ ቢሆንም የኦነግን አክራሪ ፖለቲካ በጽኑ የሚያወግዙ ሲሆን፤ በቅርቡ ከኦነግ አመራሮች ጋር የተለዋወጧቸውን ጠንካራ ቃላትም በቃለ ምልልሳችን አንስተውልናል፡፡ የዚያድ ባሬን ወረራ 42ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባልደረባችን ይርጋ አበበ በሻለቃ ዓሊ በርኬ መኖሪያ ቤት ተገኝቶ ያደረገውን ሰፋ ያለ ቃለ ምልልስ የመጀመሪያ ክፍል ዛሬ እናቀርባለን፡፡