У нас вы можете посмотреть бесплатно ትግራይ ውስጥ “ከሌሎች ክልሎች የበለጠ ብዙ ለፍተናል” - ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን | Tigray| dialogue commission| Ethiopia Insider или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ዛሬ ረቡዕ የካቲት 11፤ 2018 በነበረው አስቸኳይ ስብሰባቸው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ያደመጡት የፓርላማ አባላት፤ በትግራይ ሊካሄድ ታቅዶ ስለዘገየው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ጥያቄ ሰንዝረዋል። የኢዜማው ዶ/ር አብርሃም በርታ፤ በትግራይ ክልል ውስጥ ምክክሩ እንዳይደረግ “ተጽዕኖ እየፈጠረ ያለው” ማን እንደሆነ ጠይቀዋል። ክልሉ የምክክሩን ሂደት እንዳይከናወን የተደረገው፤ “በህገ ወጥ ቡድኑ፣ በምርጫ ቦርድ በተሰረዘው ህወሓት፤ ተጠልፎ፣ ተጠርንፎ ተይዞ ነው [ወይ]?” ሲሉም ተጨማሪ ጥያቄ አክለዋል። “ይሄ ከሆነ የፌደራል መንግስትም ትልቅ ኃላፊነት አለበት። ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ብቻ የሚተው አይደለም” ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረሥላሴ፤ የትግራይ ጉዳይ “ረጅም ጊዜ እንደወሰደባቸው” አምነዋል። ኮሚሽኑ በምክክር ሂደቱ ወቅት በሌሎች ክልሎች በአማካኝ ሶስት ጊዜ ግንኙነት እንደሚያደርግ የጠቀሱት ምክትል ኮሚሽነሯ፤ በትግራይ ክልል ግን 20 engagement ማድረጋቸውን በአጽንኦት አንስተዋል። “ትግራይ ውስጥ engage እያደረግን ሃሳብ እየተለዋወጥን ነው የቆየነው። ትግራይ ውስጥ ምንም ስራ አልተሰራም ማለት አይቻልም። ከሌላ ክልል በበለጠ ብዙ ለፍተናል” ሲሉም ኮሚሽነር ሂሩት ሁኔታውን አስረድተዋል። ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል የያዘው እቅድ እንዳልተሳካ ያመለከቱት ምክትል ኮሚሽነሯ፤ የአጀንዳ ማሰባሰቡን ለማካሄድ ሌላ አማራጭ እንደሚከተል ተናግረዋል። ዋና ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያም በሪፖርታቸው የትግራይን ክልል ጉዳይ በሰፊው ዳስሰዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) --------------------------------------------------------------------------------------------------------------------- የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦ ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider