У нас вы можете посмотреть бесплатно DW Amharic የጥር 29 ቀን 2018 የዓለም ዜና или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
የጥር 29 ቀን 2018 የዓለም ዜና • ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል የበረታውን ውጥረት ለመፍታት “የሰከኑ ውይይቶች” እንደሚያስፈልጉ አሳሰበች። • የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በመጪው ግንቦት በሚካሔደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እንደማይሳተፉ አስታወቁ። • በደቡብ ሱዳን ጆንጌሌ ግዛት የታጠቁ ወሮበሎች ትላንት ሐሙስ ሕጻናት አድን የተባለ የብሪታኒያ የግብረ-ሰናይ ድርጅት ጤና ጣቢያ ማውደማቸውን፣ ቢሮውን ማጋየታቸውን እና መዝረፋቸውን ተቋሙ አስታወቀ። • በምሥራቅ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሚገኘው የኪሳንጋኒ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት “የሽብር ድርጊት” ሊባል እንደሚችል የአፍሪካ ኅብረት አስታወቀ። • በፓኪስታን ዋና ከተማ ኢዝላማባድ በአንድ መስጂድ ውስጥ አጥፍቶ ጠፊ በፈጸመው ጥቃት 31 ሰዎች ሲገደሉ ከ170 በላይ ቆሰሉ። • የሩሲያ ጦር ሠራዊት የወታደራዊ ሥለላ ምክትል ኃላፊ ዛሬ በሞስኮ በጥይት ተመተው ቆሰሉ። ሉቴናንት ጄኔራል ቭላዲሚር አሌክሴዬቭ በሰሜናዊ ሞስኮ በሚገኝ የመኖሪያ ሕንጻ በተደጋጋሚ በጥይት ከተመቱ በኋላ ሆስፒታል ገብተዋል። • ዩናይትድ ስቴትስ ከ14 ዓመታት በፊት በሊቢያ በሚገኝ ኤምባሲዋ ላይ በተፈጸመ ጥቃት እጁ አለበት ያለችውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር እንዳዋለች የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ። • የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርስ የኢራን መሪዎች ከአሜሪካን ጋር ብርቱ ድርድር ማድረግ እንደሚኖርባቸው ጥሪ አቀረቡ።