У нас вы можете посмотреть бесплатно አካል ጉዳተኝነት ያላገደው ስራ ፈጠሪ ወጣት- ሀይልሽ ሞደፊኬሽንና ብረታ ብረት ስራ или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
ሐይልሽ አጠቃላይ ሞደፊኬሽንና ብረታብረት ኢንተርፕራይዝ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሚገኝ የባጃጅና የሞተር ብስክሌቶችን ሞዲፊኬሽንና ልዩ ልዩ የብረታብረት ስራ እየሰራ የሚገኝ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡ ወጣት ሐይልሽ ገ/ስላሴ የሐይልሽ አጠቃላይ ሞደፊኬሽንና ብረታ ብረት ስራ መስራችና ባለቤት ነው፡፡ ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል ሀገረ ሰላም ከተማ ሲሆን ስራውን የጀመረውም በሀገረሰላም በለጋነት እድሜው ብስክሌት በማከራየትና በመጠገን ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥም የቤተሰቦቸ እገዛ ቢኖርም ለአንድ አፍታ እንኳን አካል ጉዳተኛ መሆኔን ለአእምሮዬ ነግሬው አላውቅም የሚለው ሐይልሽ ማነኛውም ሰው የሚሰራውን ስራ ሁሉ መስራት እንደሚችልም ይናገራል፡፡ ለመስራት ዋናው አእምሮ (ጭንቅላት) እንደሆነ የሚናገረው ሐይልሽ ብስክሌት ከማከራየትና ከመጠገን በተጨማሪ የብረታ ብረት ስራዎች ማለትም በርና መስኮቶች በመስራት እዛው በሀገረ ሰላም ስራውን ማስፋፋት እንደጀመረ አብራርቷል፡፡ አካል ጉዳተኞች ከተመቻቸላቸውና ከሰለጠኑ የማይችሉት ወይም የማይሰሩት ነገር እንደሌለ የማሳየት ትልቅ ህልም ስለነበረው እሱን እውን ለማድረግ በ2010 ዓ.ም በክልሉ ዋና ከተማ በሆነችው ወደ መቐለ ከተማ በመምጣት ሐይልሽ ሞደፊኬሽንና ብረታ ብረት ስራ በሚል ኢንተርፕራይዝ አቋቋመ፡፡ መንግስት ሀሳቡን እውን ለማድረግ ባመቻቻለት የመስሪያ ቦታ የባጃጅ በርና ቦዲ እንዲሁም ሞተር ብስክሌቶችን ደንበኞች በሚፈልጉት መንገድ የሞዲፊኬሽን ስራ በተለይም ለአካል ጉዳተኞች እንዲስማሙ በማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ ስራ ለመስራት የአእምሮ ዝግጁነትን ይጠይቃል እንጂ አካል ጉዳተኛ መሆን የሚያግደን ነገር እንደሌለ እኔ ተምሳሌት ነኝ የሚለው ሃይልሽ ኢንተርፕራይዙ አሁን ላይ ለዘጠኝ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠርና ካፒታሉን 20 ሚሊየን ብር ማድረስ መቻሉን ተናግሯል፡፡ ሐይልሽ በልምድ በአገኝው ሙያና ባለው የፈጠራ አቅም ከብስክሌት ጥገና አሁን እስከደረሰበት የሞድፊኬሽን ስራ ድረስ ለስራው ለውጥና እድገት እየተጋ ያለ ለሌሎች የስራ እድል የፈጠረ ወጣት ነው፡፡ መንግስት አካል ጉዳተኞችን በልዩነት መደገፍና ወደ ስራ እንዲገቡ ማበረታታት አለበት የሚለው ሃይልሽ ለኢንተርፕራይዙ ከመንግስት የማሽን፣ የፋይናንስና የገበያ ትስስር ድጋፍ እንደሚያስፈልገውም ጠይቋል፡፡ በቀጣይ ስራውን በማስፋፋት በተለይም ለአካል ጉዳተኞች ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠርና የማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ለመክፈት እቅድ እንዳለው የኢንተርፕራይዙ ባለቤት ወጣት ሐይልሽ ገልጿል፡፡ 👉አድራሻ፡- ሐይልሽ ሞደፊኬሽንና ብረታ ብረት ስራ በትግራይ መቐለ ከተማ ☎️ ስልክ፡- 09-14-24-05-25