У нас вы можете посмотреть бесплатно ዓላማ መር ህይወት- ቀን 14_Purpose driven Life - Day 14_ alama mer hiywet- ken 14 или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
14ተኛ ቀን እግዚአብሔር የራቀ ሲመስል "ፊቱን ከያዕቆብ ቤት የሸሸገውን እግዚአሔርን እጠብቃለሁ እርሱንም ተስፋ አደርጋለሁ::" ኢሳ. 8-7 ምንም ይምሰልህ ምን ፣እግዚአብሔር እዉን፡፡ ነገሮች በመልካም ክንውን ላይ ባሉ ጊዜ ፣ማለት እግዚአብሔር ምግብ ፣ጓደኞች ፣ቤተሰብ ጤና እና ደስ የሚሉ ሁኔታዎችን ሲሰጥህ እሱን ማምለኩ ቀላል ነዉ፡፡ነገር ግን ሁኔታዎች ሁል ጊዜ ደስ የሚሉ አይደሉም፡፡እንዲህ ባለዉ ጊዜ እግዚአብሔር የምታመልከዉ እንዴት ነዉ?አንድ ሚሊዮን ኪሎ ሜትር ያህል የራቀ ሲመስልህ ምን ታደርጋለህ? ✅የአምልኮ ጥልቀት መለኪያዎች ፣በህመም ጊዜ እግዚአብሔርን ማክበር ፣በመከራ ጊዜ ማመስገን ፣በፈተና ወቅት በእርሱ መታመን ፣በስቃይ ጊዜ ራስን ለእርሱ ማስረከብ ፣እና የራቀ በሚመስልበት ጊዜ እሱኑ መዉደድ ናዘዉ፡፡ ወዳጅነት ብዙ ጊዜ በዝምታ ይፈተናል ፡፡ሰዉ በአካል በመራራቅ ወይም ለመነጋገር ባለመቻል ይለያያል ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ባለህ ወዳጅነት ፣አብዛኛዉ ጊዜ ወደ እርሱ የቀረብህ መስሎ አይሰማህም፡፡ እግዚአብሔር ፣ከእርሱ ጋር ያለህን ወዳጅነት ለማሳደግ ሲል ፣የተወህና የረሳህ በሚመስል ጊዜ ዓማካይነት ወዳጅነታችሁ ይፈትነዋል፡፡ እነዚህ የነፍስ ሌሊቶች ወይም የልብ ክረምቶች ልንላቸዉ ምንችለዉ ጊዜያት ናዘዉ፡፡ ከእየሱስ ቀጥሎ ዳዊት ከማንም ይልቅ የእግዚአብሔር የቅርብ ወዳጅ ሳይሆን አይቀርም ፡፡እግዚአብሔር "እንደ ልቤ የሆነ ሰዉ"1ሳሙ 13:14 ዳዊት እንኳን እግዚአብሔር ሆይ ለምን እንደዚህ እርቀህ ቆምህ?በመከራ ጊዜስ ለምን ድምፅህን አጠፋህ ?መዝ 10:1 አምላኬ አምላኬ ለምን ተዉኸኝ መዝ 22:1 እግዚአብሔር አንዳንዴ ፊቱን ከእኛ የሚሰዉር መሆኑን ያምናል ፡፡ "እነሆ ወደ ፊት እሄዳለዉ እርሱም የለም ፤ወደ ኃላም እሄዳለሁ እኔም አላስተዉልም ወደ ሚሰራበት ወደ ግራ ብሄድ አልመለከተዉም በቀኜም ይሰወራል አላየዉምም ኢዮ 23:8 ክርስቲያኖች ዛሬ በአምልኮ ዉስጥ የሚፈፅሙት በጣም የተለመደ ስሕተት ፣ከእግዚአብሔር ይልቅ አንድ አይነት ልምምድ መፈለጋቸው ነዉ፡፡አንድ አይነት ስሜት ይፈለጋሉ ፤ከሆነላቸዉ ስለ ማምለካቸዉ እርግጠኛ ይሆናሉ፡፡ይህ ስተት ነዉ፡፡ የእግዚአብሔር በሁሉም ስፍራ መገኘትና ፣በህልዉናዉ መገለጥ ሁሉቱ የተለያዩ ነገሮች ናዘዉ፡፡አንደኛዉ የተረጋገጠ እዉነት ሲሆን ፣ሌላዉ ብዙ ጊዜ ስሜት ነዉ፡፡መገኘቱ በማይሰማህ ጊዜ እንኳን እግዚአብሔር በቅርብህ አለ፡፡ መገኘቱ ደግሞ በስሜት ሊገለጥ የማይቻልና እጅግ ታላቅ ነዉ፡፡ እምነትህ በጣም እንዲያድግ የሚያደርጉት ሁኔታዎች ፣ሕይወትህ ሲመሰቃቀልና አግዚአብሔር ፍፁም ልታገኘው በማትችለዉ ወቅት ያለህ በሚመስልህ ጊዜ ያሉት ናቸዉ፡፡ኢዮብ ይህ ደርሶበታል ቤተሰቡን ስራዉን ጤናውንና ያለዉን ነገር ሁሉ በአንድ ቀን ዉስጥ አጣ፡፡ከሁሉ ተስፋ የሚያስቆርጠዉ ነገር ደግሞ ሰላሳ ሰባት ምዕራፍ ሙሉ እግዚአብሔር ዝም ማለቱ ነዉ፡፡ እግዚአብሔር የራቀ ሲመስል የሚሰማህን ስሜት ሁሉ አራግፈ ንገረዉ ፡፡በማይለወጠዉ በእግዚአብሔር ማንነት ላይ አተኩር እግዚአብሔር መልካም ነዉ ይወደኛል ከኔ ጋር አለ ያለሁበትን ሁኔታ ያዉቃል ይጠነቀቅልኛል ለሕይወቴ መልካም እቅድ አለዉ እያልክ ስለ እግዚአብሔር የምታዉቀዉን ዘላለማዊ እዉነት ለአንተነትህ አስታዉሰዉ ፡፡ እግዚአብሔር በብርሃን የነገረህን በጭለማ አትጠራጠር፡፡ እግዚአብሔር የራቀ ሲመስል እንዴት ነዉ እርሱ ከኔ ጋር ያለ መሆኑ እዉነት ላይ ለማተኮር የምችለው ???? “እግዚአብሔር ከቶ አልተዉህም ፤በፍፁም አልጥልህም ብሎአልና” ዕብ 13:5 በሪክ ዋረን አላማ መር ህይወት