У нас вы можете посмотреть бесплатно ዓላማ መር ህይወት- ቀን 28_Purpose driven Life - Day 28_ alama mer hiywet- ken 28 или скачать в максимальном доступном качестве, видео которое было загружено на ютуб. Для загрузки выберите вариант из формы ниже:
Если кнопки скачивания не
загрузились
НАЖМИТЕ ЗДЕСЬ или обновите страницу
Если возникают проблемы со скачиванием видео, пожалуйста напишите в поддержку по адресу внизу
страницы.
Спасибо за использование сервиса ClipSaver.ru
28 ቀን ጊዜ ይወስዳል "ለሁሉም ጊዜ አለዉ ፤ከሰማይ በታችም ለሆነዉ ነገር ሁሉ ጊዜ አለዉ፡፡" መክ 3:1 ወደ መብሰል (እድገት )የሚያደርስ አቋራጭ መንገድ የለም፡፡ ሙሉ ሰዉ ወደ መሆን ለማደግ አመታት ይወስድብናል ፡፡ፍሬ አድጎ ለመጎምራት አንድ ወቅት ይወስድበታል፡፡ የመንፈስ ፍሬም እንዲሁ ነዉ፡፡ ክርስቶስን የመምሰል ባህሪይን በጥድፊያ ለማግኘት አይቻልም፡፡ መንፈሳዊ እድገት እንደ አካላዊ እድገት ጊዜ ይወስዳል፡፡ ፍሬ ቶሎ እንዲጎመራ ባደረከዉ ቁጥር ጣዕሙን ያጣል ፡፡ 👌 በምን ያህል ፍጥነት እንድናድግ እኛ ስንጨነቅ ፣እግዚአብሔር የሚያሳስበዉ ግን ምን ያህል ብርቱ ሆነን ማደጋችን ነዉ፡፡ እግዚአብሔር ሕይወታችንን የሚመለከተዉ ፣ከዘላለም አና ለዘላለም ከሆነ አላማዉ አንፃር ስለሆነ በፍፁም አይጣደፍም፡፡ ደቀ መዝሙርነት ክርስቶስን የመምሰል ሂደት ነዉ፡፡ "በእናንተ መልካምን ስራ የጀመረው እስከ እየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመዉ ይህን ተረድቻለዉ፡" ፊል 1:6 የመጨረሻ መድረሻህ ክርስቶስን መምሰል ሲሆን ፣ጉዞህም እስከ ሕይወትህ ፍፃሜ ነዉ፡፡ ✅እስካሁን ድረስ ይህ ጉዞ ፣እምነትን(በአምልኮ) ፣አካልነትን (በህብረት )እናመሆንን (በደቀ መዝሙርነት) ፣የሚያካትት መሆኑን ተመልክተናል፡፡ እግዚአብሔር እርሱን በመምሰሉ ሂደት በየእለቱ በትንሹ እየጨመርክ እንድታድግ ይፈልጋል ፡፡ "የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እዉቀትን ለማግኘት የሚታደሰዉን አዲሱን ሰዉ ለብሳችሁታል፡፡" ቆላ 3:10 ዛሬ አእሯችን ፍጥነት በሚሹ ጉዳዮች ተሞልቷል፡፡እግዚአብሔር የሚፈልገው ፣ከፍጥነት ይልቅ ብርታትና ፅናት ሲሆን ፣እኛ የምንፈልገው ደግሞ ፣ቅጽበታዊ ጥገና ፣አቋራጭ መንገድ ፣ፈጣን መፍትሄ ነዉ፡፡ ለምንድነው ረጅም ጉዞ የሚወስደዉ?? ምንም እንኳን እግዚአብሔር በቅጽበት ሊለዉጠን የሚችል ቢሆንም ፣በቀስታ ሊያሳድገን መርጦአል፡፡ እግዚአብሔር እስራኤላዉያን ከጠላቶቻቸው ብዛት የተነሳ እንዳይደነግጡ የተስፋይቱን ምድር "አምላክህም እግዚአብሔር እነዚህን አህዛብ በጥቂት በጥቂቱ ከፊትህ ያወጣቸዋል ፤የምድረበዳ አራዊት እንዳይበዙብህ አንድ ጊዜ ታጠፋቸዉ ዘንድ አይገባህም ፡፡" ዘዳ 7:22 በእኛም ሕይወት እየጨመሩ በሚሄዱ ደረጃዎች መሥራት ነዉ የሚመርጠዉ፡፡ 👌ያለ ለዉጥ እድገት የለም ፣ፍርሃት ወይም ማጣት የሌለበት ለዉጥ የለም ፤ያለ ስቃይም መሸነፍ የለም፡፡ ባህሪይህ የልማዶችህ ድምር ዉጤት መሆኑን አስታዉስ ደግነት የማድረግ ልማድ ከሌለህ ፣ደግ ነኝ ለማለት አትችልም፡፡ ደግነትን የምታሳየው ደግ ልሁን ብለህ ሳታስብ ነዉ፡፡ እዉነተኛነት የሁልጊዜ ልማድህ ካልሆነ ፣ቅን ነኝ ብለህ ለመናገር አትችልም ፡፡ የክርስቶስን የሚመስሉ ባህርያትን ማዳበሪያ የሆነ አንድ መንገድ ብቻ አለ፡፡ ባህሪያቱን ተለማመዳቸዉ ፣ያ ደግሞ ጊዜ ይወስዳል!ልማዶች በቅፅበት አይመጡም:: ማደግህ በነገር ሁሉ ይሁን 1ጢሞ 4:15 እግዚአብሔር በሕይወትህ በመስራት ላይ መሆኑ በማይሰማህ ጊዜ እንኳን በስራ ላይ መሆኑን እመን፡፡በመንፈሳዊ ህይወት ዉስጥም ወቅቶች አሉ ፡፡አንዳንድ ጊዜ አጭርና ኃይለኛ ፍጥነት ያለው እድገት (የፀደይ ወራት) ፣ቀጥሎ ደግሞ ስር የምንሰድበት የፈተና ወቅት (መከርና ክረምት ) ፣ይኖራሉ፡፡ በየጊዜው የምትቀስማቸዉ ትምርቶች የምትጽፍበት ማስታወሻ ደብተር አዘጋጅ ፡፡ ከእግዚአብሔር ሆነ ከራስህ ጋር ትግስት ይኑርህ ፡፡በሕይወት ተስፋ ከሚያስቆርጡ ነገሮች አንዱ የእግዚአብሔር የጊዜ ሰሌዳ ከእኛ ጋር ብዙ የማይመሳሰል መሆኑ ነዉ፡፡ በሕይወት ያለህ ዕድገት አዝጋሚ መምሰሉ ተስፋ መቁረጥ የሰማህ ይሆናል ፡፡ያን ጊዜ እግዚአብሔር በፍፁም በፍፁም የማይጣደፍ ፣ነገር ግን ፣በጊዜዉ የሚደርስ መሆኑን አስታዉስ ፡፡ ✅እግዚአብሔር እንጉዳይ ሲፈጥር በአንድ ሌሊት ግዙፍ ግንድ ሲሰራ ግን በመቶ ዓመት ያደርገዋል ፡፡ ተስፋ አትቁረጥ መዘግየት በእግዚአብሔር ዘንድ ቃሉን መሻር አይደለም፡፡ የቀረህን ብቻ ሳይሆን ፣እዚህ ለመድረስ የተጓዝከዉን እርቀት አስታዉስ፡፡ለመገኘት የምትፈልገዉ ፣ወይም እነበርህበት ስፍራ አይደለህም፡፡ 😄ቀንድ አዉጣ እንኳን ያለ መታከት ተጉዞ ኖህ መርከብ ገብቶአል፡፡ 🔔በየትኛው የመንፈሳዊ ዕድገት አቅጣጫ ነዉ ይበልጥ ታጋሽና ትጉህ መሆን የሚኖርብኝ?? በሪክ ዋረን አላማ መር ህይወት